በ19ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የህዳሴ ዋንጫ የምድብ ሁለት ሁለተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ኢትዮ ኤሌክትሪክን 1 ለ 0 ረቷል።
ውጤቱንም ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና ምድቡን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ ሽንፈት ያስተናገደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ የሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ተሸጋግሯል።
ከጨዋታዉ በኋላ የኢትዮጵያ ቡናው ዋና አሰልጣኝ አቢይ ካሳሁን በነበረው የድህረ ጨዋታ ቆይታ ወቅት ስለ ጨዋታው የነበረውን ምልከታ እንዲህ ገልጿል።
“የመጀመሪያው አጋማሽ ላይ ትንሽ ቀዝቃዛ ሆነን ነበር የጀመርነው ፤ የባለፈው አይነት መነሳሳት አልነበረም። ሁለተኛው አጋማሽ በርካታ ነገሮች ተሻሽለን በተለይ መካለከሉን ፕሬስ አድርገን በማግቃቱም በደንብ በቁጥር እየበዛን ቀደ ጎልም በርካታ ጊዜ ደርሰናል። ከዕረፍት በኋላ ባስተካከልነው መሰረት ማሸነፍ ይገባናል ብዬ አስባለሁ።”
- ማሰታውቂያ -

ውድድሩን እንደ አቋም መለኪያ መሆኑን ያስታወሰወሰ አሰልጣኝ አቢይ በተለይም በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይረው የገቡ በጣም ጥሩ ነገር ሰጥተውናል በማለት በሊጉ ላይ ማስተካከል የሚገባቸውን ክፍተተም መገንዘባቸውን ተናግሯል።
አክሎም ከሁለቱም ጨዋታዎች አንፃር በዛሬው ጨዋታ በሁለተኛው አጋማሽ በነበረው እንቅስቃሴ ደስተኛ ነኝ ሲል ገልጿል።
በግማሽ ፍፃሜው በሸገር ደርቢ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር መገናኘታቸውን አስመልክቶም አሰልጣኝ አቢይ ይህን ብሏል።
“ይሄ የመዘጋጃ ጨዋታ ነው። በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታ እንገናኛለን ስለዚህ ይህንን ጨዋታ በይበልጥ እውነት ለመናገር እንደ መዘጋጃ ውድድር ስለሆነ አሁንም ያለንን በሊጉ ላይ ምን ማድረግ እንዳለብን እንደማንኛውም ጨዋታ በዛ መልኩ ነው የምናየው።”
የኢትዮ ኤሌክትሪኩ ዋና አሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ በበኩሉ ስለ ጨዋታው ተከታዩን ተናግሯል።
“ጨዋታው በጣም ጥሩ ነው። የምንፈልገው እና ማድረግ የምንፈልገውን ነገር አድርናል። የተሻለ ነገር ብዙ ነገሮች አድርገናል ግን ያው በመጨረሻ ደቂቃ ላይ በራሳችን የጥንቃቄ ጉድለት ጎል ገብቶብናል። ግን ያው እግር ኳስ ነው እንጂ የመጀመሪያው አጋማሽ ሁለተኛው አጋማሽም በጣም ጥሩ ነው። ያሰብነው እና ማድረግ ያለብንን ነገሮች አድርገን ጥሩ ነገር አይቼባቸዋለሁ ተጫዋቾቼ ላይ እላለሁ።”
“ባለህ ነው የምትሰራው አንድ ሁለት ተጫዋቾች እዚህ ላይ አስገባለሁ። ሲቲ ካፕ ያለህን ድክመት ጠንካራ ጎን እና ደካማ ጎን የምታይበት ነው።አቅም ኣለቸው ልጆቼ በጣም ተጫውተዋል ጥሩ ነገር ሰርተዋል። የሳቷቸው ኳሶች በመጓጓት ነው ግን በተገላቢጦሽ ደግሞ የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ በቅንጅት ስህተት እና በአንዳንድ ተጫዋቾች ትኩረት ማነስ ጎል ገብቶብናል። ያንን ካስተካከልን ጥሩ ቡድን ነው ብዬ አስባለሁ።”


