የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ኤፊ ኦኑራ በእንግሊዝ በፕርሚየር ሊጉ ሀላፊዎች የፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያው የእኩልነት እና ብዝሃነት ኃላፊ በመሆን ለመሾም ከስምምነት መደረረሳቸው ይፋ ተደርጓል ።
የ 53 ዓመቱ የቀድሞው የ ሀደርስፊልድ እና ግሊንግሀም ክለብ ተጫዋች ኤፊ ኦኑራ ከዚህ ቀደም የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማህበር ላይ የእኩልነት ሀላፊ በመሆን መስራታቸው ይታወሳል ።
የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ይህን ሹመት ለ ኤፊ ኦኑራ ከመስጠታቸው አስቀድሞ የተለያዩ ብቃቱ ያላቸውን ሰዎች በ 2020 የፈረንጆች አቆጣጠር ጀምሮ ለመቅጠር ሲሰሩ ወቅታዊው የኮሮና ቫይረስ ጉዳዩን እንዳዘገየው ተገልጿል ።
ኤፊ ኦኑራ ከመጪው ወርሀ ሚያዚያ ጀምሮ ስራቸውን እንደሚጀምሩ ተገልጿል ።
- ማሰታውቂያ -
ኦኑራ ከዚህ ቀደም ጥቁር እንዲሁም ከ እስያ ሀገራት አሰልጣኞች የሻምፒየንሺፑን ክለቦች እንዲቀላቀሉ በማበረታታት ትልቅ ሚና መጫወት ችለዋል ፡፡


