መነሻ ገጽ አርሲ ነገሌ ነገሌ አርሲ በነፃ ዝውውር ናይጄሪያዊ አጥቂ አግኝቷል
አርሲ ነገሌዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎች

ነገሌ አርሲ በነፃ ዝውውር ናይጄሪያዊ አጥቂ አግኝቷል

አጋራ
አጋራ

በኢራቅ ሊግ ቆይታ የነበረው አጥቂ ነገሌ አርሲን ይቀላቀላል።

ኪቲካ ጀማን በዝውውሩ የመዝጊያ ቀን ከመቐለ 70 እንደርታ ያስፈረመው አዲስ አዳጊው የሊጉ ክለብ ነገሌ አርሲ በአጋማሹ ሁለተኛ ፈራሚው ናይጄሪያዊውን የ28 አመት ዕድሜ አለው የተባለውን አጥቂውን ኒድፍሬክ ኢዶ ኢፍዮንግን ለማስፈረም በመስማማቱ ነገ ወደ ኢትዮጵያ ይገባል።

በሀገሩ ክለብ አቢያ ኮሜት እግር ኳስን ጀምሮ በመቀጠል አቢያ ዋሪሪየርስ እና አኩዋ ስታርስ በተባሉ ክለቦች ግልጋሎት ሰጥቶ ወደ ሊቢያ አምርቶ ለአል-ሀሊ በሞሮኮው ኦሎምፒክ ሳፊ በኢራቁ አልቁማል አልጃህ እና አልናፋት ከተጫወተ በኋላ በድጋሚ ወደ ሀገሩ ተመልሶ ለሪቨር ዩናይትድ በ2024/25 የውድድር ዘመን ደግሞ ወደ ኢራቅ በመመለስ ለኒው ሮዝ እንዲሁም በያዝነው አመት ደግሞ በዛው በኢራቅ ትልቁ ሊግ ኢራቅ ስታርስ ሊግ ላይ በአል ሄዶድ እየተጫወተ የቆየው እና ጋቶች ፓኖም ወደ ሳውዲ ከማምራቱ በፊት በአልናጃፍ ቆይታው አንድ ጎል ባስቆጠረበት እና በድምሩ ከ203 ጎል አስቆጣሪ ተጫዋቾች ባሉበት ሊግ በጎል አስቆጣሪ ዝርዝር ውስጥ የሌለው ይህ አጥቂ አዲሱ የነገሌ አርሲ ተጫዋች ለመሆን ተቃርቧል።

ኢራቃዊው መሐመድ አሊ በ27 ጎሎች በሚመራበት የኢራቅ ሊግ ነገሌን የሚቀላቀለው የናይጄሪያዊው አጥቂ ክለብ የሆነው አል ሁዶድ ከ20 ክለቦች 19ኛ ላይ ተቀምጦ ላለመውረድ እየተጫወተ ይገኛል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...