መነሻ ገጽ ኢትዮጵያን በውጪ በኮንሶ ተወልዶ በፈረንሳይ እየተጫወተ የሚገኘው ተከላካይ
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

በኮንሶ ተወልዶ በፈረንሳይ እየተጫወተ የሚገኘው ተከላካይ

አጋራ
አጋራ

ወደ ልጅነት ክለቡ ኖንት ወይም ኮሞ የመዛወር ተስፋ ያለው ተከላካይ ማነው ?

የተወለደው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በኮንሶ ወረዳ ገዋዳ ተብላ በምትጠራ ቦታ ሲሆን ዕድገቱ የሆነው ግን በፈረንሳዩዋ የኖንትስ ከተማ ውስጥ ነው። በቀኝ መስመር ተከላካይነት አልያም ደግሞ ወደ ቀኝ መስመር የማጥቃት ባህሪን ተላብሶ የሚጫወተው ማቲዮስ አማኑ ፒሊፕ እግር ኳስን የጀመረው በሚኖርባት ከተማ ባለችው እና በፈረንሳይ ሊግ ዋን ላይ በምናውቀው ኖንት ክለብ ውስጥ ነው።

በአሁኑ ሰዓት ሀያ አመቱን የደፈነው እና እና በኖንትስ ከ17 እና ከ19 አመት በታች እንዲሁም ከወር በፊት ከተለያየው ሄላስ ቬሮና ከ19 እና ከ20 አመት በታች ቡድን ውስጥ መጫወት ችሏል። በልጅነት ክለቡ ኖንት ከ21 አመት በታች ወይንም በሴስ ፋቭሪጋስ በሚሰለጥነው ኮሞ ከ21 አመት በታች ቡድን በቀጣይ ክረምት እንደሚቀላቀል የሚጠበቀው ይህ ተጫዋች ለተወለደባት ኢትዮጵያ መጫወትን እንደሚፈልግ ባደረኩት ቆይታ አጫውቶኛል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...