መነሻ ገጽ አፍሪካ ዋንጫ ዋልያዎቹ ከሜዳቸው ውጪ ድል ቀንቷቸዋል
አፍሪካ ዋንጫአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ ከሜዳቸው ውጪ ድል ቀንቷቸዋል

አጋራ
አጋራ

በገለልተኛ ሜዳ ሞሮኮ ላይ ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን በአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የገጠመው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን 3ለ0 አሸንፏል።

በሦስቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አዘጋጅነት ለሚደረገው ለ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ቀደም ብሎ በሚደረገው የምድብ የማጣሪያ ድልድል ውስጥ ለመካተት በቅድመ ማጣሪያ መርሀ-ግብርን ሞሮኮ ላይ ከሳኦቶሚ እና ፕሪንስፔ ጋር የመጀመሪያ ማጣሪያውን ያደረገው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

በመጀመሪያው አጋማሽ በይበልጥ ወደ ፊት ተስቦ መጫወትን መርጦ የታየው ዋልያው 23ኛው ደቂቃ ላይ የሳኦቶሜ ተከላካዮች በቅብብል ወቅት ወደ ግብ ዘቡ ወደ ኋላ የመለሱትን ኳስ ቀድሞ ያገኘው ከነዐን ማርክነህ አጋጣሚዋን መረቡ ላይ በማሳረፍ ቡድኑን መሪ ማድረግ ሲችል 32ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ በተከላካዮች የቅብብል ስህተት ከሳኦቶሚዎች እግር ስር ኳስን ያገኘውን አቤል ያለው በድንቅ አጨራረስ መረቡ ላይ ሁለተኛ ጎል አድርጓታል።

ጨዋታው ከዕረፍት ሲመለስ አሁንም ከቆሙበት ብልጫቸው የቀጠሉት ዋልያዎቹ በተለይ ተጋጣሚያቸው በድግግሞሽ ይሰሯቸው በነበሯቸው ስህተቶች ከግራ መስመር አቅጣጫ 78ኛው ደቂቃ ላይ አቤል ያለው የደረሰውን ኳስ አራት ተከላካዮችን በብልጠት አልፎ ለራሱ ሁለተኛ ለቡድኑ ሦስተኛ ጎል በማድረግ ጨዋታው 3ለ0 ፍፃሜን አግኝቷል።

የዚህ ጨዋታ የመልስ መርሀ-ግብር የፊታችን ማክሰኞ መጋቢት 22 በድሬዳዋ ስታዲየም የሚደረግ ሲሆን የድምር ውጤት አሸናፊው ወደ ማጣሪያ ድልድሉ የሚቀላቀል ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

1. ፉአድ ኢብራሂም (ኢትዮጵያ ቡና) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ...