ለጀርመኑ ህርታ በርሊን የሚጫወተውን የግራ መስመር ተከላካይ አሁን ደግሞ ወደ እናንተ ይዘን ቀርበናል።

አሁን ደግሞ የማስተዋውቃችሁ በቅርብ ጊዜያት ከጀርመን ቡንደስሊጋ በወረደው ህርታ በርሊን ክለብ ውስጥ እየተጫወ ስለሚገኘው የግራ መስመር ተከላካዩ ኤልያስ ስትራስነር ይሆናል። ከኢትዮጵያዊው አባቱ ስለ ኢትዮጵያ ታሪክን እየተማረ ማደግ የቻለው እና በጀርመኑ ኖርማኒያ እግር ኳስን በሚገባ ስልጥኖ የወጣው የ21 አመቱ ተጫዋች በመቀጠልም በጀርመን ሀያል ከሚባሉ ክለቦች ውስጥ ስሙ በሚጠራው ህርታ በርሊን ክለብ ውስጥ ከታዳጊ ቡድኑ አንስቶ የ17 እና የ18 አመት በታች ቡድኖች ውስጥ በሚገባ ተጫውቶ አሳልፏል።
ለጀርመን ከ18 አመት በታች ብሔራዊ ቡድን መለያውን ለብሶ ለመጫወት የበቃው አንድ ሜትር ከሰባ ዘጠኝ ሴንቲ ሜትር የሚረዝመው ይህው ወጣት የግራ መስመር ተከላካይ ስለ ኢትዮጵያ አብዝቶ ከማወቁ ባለፈ የሀገሪቱን ብሔራዊ ቡድን መለያ ለብሼ መጫወት እፈልጋለሁ ሲል ይገልፃል።
አስተያየት ይስጡ