ኢትዮጵያ እና ሳኦቶሜ የሚያደርጉትን ጨዋታ ሴኔጋላዊያን ዳኞች ይመሩታል።
የአፍሪካ ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ያለበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድኑ ከፊቱ ሁለት የደርሶ መልስ መርሀግብር ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ያለበት ሲሆን የመጀመሪያውን የማጣሪያ ጨዋታን መጋቢት 16 ሞሮኮ በሚገኘው ኤል አብዲ ኤልጃዲዳ ስታዲየም አመሻሽ 10 ሰዓት ላይ ሲያከናውን አራት ሴኔጋላዊያን ዳኞች ጨዋታውን እንዲመሩት በካፍ መመረጣቸውን ሀትሪክ ስፖርት ማረጋገጥ ችላለች።
በዋና ዳኝነት ከ2019 ጀምሮ በኢንተርናሽናል ዳኝነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ኤልሀጂ አማዱ ሲ በመሐል ዳኝነት በረዳት ዳኝነት ደግሞ የሀገሩ ልጆች ማማዱ ናጎም እና መሐመድ ፎል አራተኛ ዳኛ ደግሞ አዳልበርት ዲዮፍ የጨዋታው ታዛቢ ደግሞ ማጋሳ ሲዴ ቤካዬ ከማሊ መሆናቸውን አውቀናል።
የመልሱ ጨዋታ መጋቢት 22 በድሬዳዋ አለምአቀፍ ስታዲየም ይደረጋል።
አስተያየት ይስጡ