የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ አምስተኛ ጨዋታውን ከግብፅ አቻው ጋር ያደርጋል።
መጋቢት 12/2017 በሞሮኮ ካዛብላንካ ከተማ ላርቢ ዛውሊ ስታድየም የሚደረገውን ይህን ጨዋታ የሞሪሸስ እና ሲሸልስ ዜግነት ባላቸው ዳኞች ይመራል ።
ሞሪሸሳዊው የ39 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ፓትሪስ ሚላዛሬ ጨዋታውን በዋና ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል።
ፓትሪስ ሚላዛሬ በዘንድሮው የውድድር ዘመን ቲፒ ማዜምቤ ከኤምሲ አልጀርስ እንዲሁም ያንግ አፍሪካ ከኤምሲ አልጀርስ ያደረጓቸውን የአፍሪካ ቻምፕየንስ ሊግ ጨዋታዎች በዋና ዳኝነት መርተዋል።
- ማሰታውቂያ -
በተጨማሪም በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጋና ከሱዳን እንዲሁም ሊብያ ከቤኒን ያደረጓቸውን ጨዋታዎች መምራት ችለዋል።
ፓትሪስ ሚላዛሬ ከ2021/22 ጀምሮ በድምሩ 18 አህጉራዊ የብሔራዊ ቡድን እና የክለብ ውድድር ጨዋታዎችን መርተው 47 የማጠንቀቂያ የቢጫ ካርዶችን(2.61/በጨዋታ) ለተጫዋቾች አሳይተዋል።
በተጨማሪም የሞሪሸየስ እና የሲሸልስ ዜግነት ያላቸው ዳኞች በረዳት ዳኝነት ጨዋታውን ሲመሩ አራተኛ ዳኛውም ከሲሸልስ ናቸው።


