By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “መከላከሉን አንንቅም ፤ ማጥቃቱንም አንተውም” “ከጨዋታ መንገድ ጋር በተያያዘ…እነ ሱራፌል ፣ ከነዓን እና ጋቶችን አላካተተንም” “በሂደት ለውጦችን ታያላችሁ” “አቡበከር ጤናማ ከሆነ ጥሩ ነገር መስራት የሚችል ልጅ ነው” አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንዜናዎችየአለም ዋንጫ ማጣሪያ

“መከላከሉን አንንቅም ፤ ማጥቃቱንም አንተውም” “ከጨዋታ መንገድ ጋር በተያያዘ…እነ ሱራፌል ፣ ከነዓን እና ጋቶችን አላካተተንም” “በሂደት ለውጦችን ታያላችሁ” “አቡበከር ጤናማ ከሆነ ጥሩ ነገር መስራት የሚችል ልጅ ነው” አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 12 months ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የቡድኑን ዝግጅት በተመለከተ በጋዜጣው መግለጫው በርከት ያሉ ነጥቦች አንስቷል።

በተለይም በተደጋጋሚ የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን በደንብ ተመልክተናል ያለው አሰልጣኝ መሳይ በራሳችን ላይም ከዚህ ቀደም የነበሩብንን ክፍተቶች በመለየት ስራዎችን ሰርተናል ብሏል።

በጋራ በሚሰሩ ነገሮች ላይ በጣም ትኩረት ሰጥተን ሰርተናል በማጥቃትም ሆነ በመከላከል ወቅት ማድረግ ስለሚገቡን ነገሮች በተናጠል ልምምዶችን አድርገናልም ሲልም ተናግሯል።

ከአጨዋወት መንገድ ጋር በተያያዘ በ3-5-2 የጨዋታ ቅርፅ እንደሚጫወቱ የተናገሩ ሲሆን የመረጧቸው ተጫዋቾችም ለዚህ የጨዋታ መንገድ የሚሆኑ ስለመሆናቸው አብራርቷል።

- ማሰታውቂያ -

“3-5-2 ሲሆን ሶስቱ የመሀል ተከላካዮች ቆመው የሚጫወቱ አይደሉም። በተለይ ዳር ዳር ያሉትን ስንመርጥ በተወሰነ መልኩ እየሄዱ ማጥቃት የሚችሉ ተጫዋቾችን ነው የመረጥነው። በተጨማሪም በዳር እና በዳር ያሉት የመስመር ተጫዋቾች የአማካይ ባህሪ ነው ያላቸው።”

አክሎም ከግላዊ ይልቅ የቡድን ስራን ማስቀደማቸውን በመግለፅ ለመከላከል አይደለም የተዘጋጀነው ብሏል።

“ባላንስ የሆነ ነገር ነው ሰርተን የመጣነው መከላከሉንም አንንቅም ማጥቃቱንም አንተውም። ለመከላከል አይደለም የተዘጋጀነው እግር ኳስ ሁለቱንም ነገር ባላንስ አድርጎ መሄድ ይፈልጋል።”

ለዚህም የሚሆኑ ተጫዋቾችን በሁለቱ ጨዋታዎች ለመተግበር ካሰቡት ጨዋታ መንገዳቸው አንፃር በመለካት ምርጫው መደረጉን ጠቁሟል።

በአርቡ ጨዋታ የሚሆነውን ነገር ብንመለከት ጥሩ ነው ጨዋታው የሚነግረን ነገር አለም ሲል አሰልጣኝ መሳይ ገልጿል።

የግብፅ አጥቂዎችን በተመለከተም በግል ያላቸው ነገር ይታወቃል ያለው አሰልጣኝ መሳይ የመሀመድ ሳላህን ስም በመጥቀስ በጨዋታ ወቅት ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ እናውቃለን ፤ እንዴት ማቆም አለብን በሚለው ላይ በሚገባ ተዘጋጅተናል ብሏል።

ከተጫዋቾች ምርጫ መስፈርት ጋር በተያያዘ በዋነኝነት ወቅታዊ ብቃት ሲሆን የአጨዋወት መንገድ ፣ አካል ብቃት ፣ ዲሲፕሊን የመሳሰሉ ነገሮችም ከግምት ገብተው ብዙ አውጥተን አውርደን ነው ለ24 ተጫዋቾች ያደረግነው ሲል ተናግሯል።

“ከእኛ የጨዋታ መንገድ ጋር በተገናኘ የምንፈልገውን ነገር የሚሰሩ ልጆችን መርጠናል። እነ ሱራፌል ፣ ከነዓን እና ጋቶችን አላካተተንም። ያላካተትነው የምንፈልጋቸው ነገሮች አሉ ፤ በደንብ የምንፈልጋቸው የጨዋታ መንገዶች አሉ። አሁን እኛ ከምንከተለው አንፃር አላካተተንም።”

በሀገር ውስጥ የሚጫወቱ ተጫዋቾች ጥሩ ብቃት እያሳዩ ያሉ ቢኖሩም ሁሉንም መምረጥ አንችልም የተሻሉትን መርጠን በቡድኑ አካተናል ብሏል።

አቡበከር ናስርን በተመለከተም ለጨዋታው ዝግጁ መሆኑን በማንሳት ሙሉ ጤናማ ከሆነ ምን ማድረግ እንደሚችል የሚታወቅ ነው ሲል ገልፆታል።

“አቡበከርን በተመለከተ መረጃዎችን ወስደናል። ከሱ ጋርም ተነጋግረናል። ያለውን ሁኔታ ከቡድኑ ጋር እየሰራ እንደሆነ እና ጤነኛ እንደሆነ ቼክ አድርገን ነው ፤ አብሮን የመጣው። ከመጣ በኋላም የሚያሳየን ነገር ጥሩ ነገር ነው ያየንበት እኛ ከምንፈልገው ነገር አንፃር ይሰራልናል ያሉ ልጆችንም ያግዛል ብለን ነው ወደ እኛ ያካተትነው።”

የተጫዋቹ ወቅታዊ ብቃትም ጥሩ ነው ያለው አሰልጣኝ መሳይ አበቡከር ጤናማ ከሆነ ሜዳ ላይ ጥሩ ነገር መስራት የሚችል ልጅ ነው ብሏል።

“የአቡበከር ውቅታዊ ብቃትን በቅርበት ያሉ ሰዎች ሊናገሩ ይችላሉ ብዬ አስባለሁ። ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለው። ይታወቃል አቡበከር ጤናማ ከሆነ ጥሩ ነገር መስራት የሚችል ልጅ ነው። ጠንካራ ነገር የተሻለ ነገር ሊያመጣ የሚችል ጎበዝ ልጅ ነው።”

አሰልጣኝ መሳይ በተጨማሪም የቡድኑን ውጤታማነት በተመለከተ በሰጠው ግብረ መልስ በአንድ ጊዜ የሚለወጥ ነገር አይኖርም በሂደት ግን ለውጦቸን ታያላችሁ ፤ እያንዳንዱን ችግሮቻችንን አናልፍም ገምግመን እያረምን መፍትሄ ሰጥተን እንዲሁም እርማት ወስደን ነው የምንሄደው ምክንያቱም ይህ የግል ጉዳይ አይደለም የሀገር ጉዳይ ነው ብሏል።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article “እንደከዚህ በፊቱ ጎል ስንት ይገባባችኋል ተብሎ የሚሄድ ብሔራዊ ቡድን የለንም” “ቡድን አጋነን የምናይበት ነገር የለም አሁን ላይ” “ተፅዕኖ ከሚፈጥሩብን መካከል ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚፃፉ ነገሮች እንደሆኑ እኔ በግሌ አምናለሁ” አስቻለው ታመነ ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አምበል
Next Article “ከ40 እስከ 50 ሺህ ዶላር የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሚሸፍንልን ይሆናል” “በቀጣይ አምስት ወራት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሀገሩና በደጋፊው ፊት መጫወት የሚችልበት ዕድል አለው…..” አቶ ባህሩ ጥላሁን ፦ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችትግራይ ዋንጫ

ትግራይ ዋንጫ| ደቡብ ደርቢ ለፍፃሜ ያገናኘው ትግራይ ዋንጫ ነገ ፍፃሜውን ያገኛል

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 6 years ago
የጨዋታ ዘገባ | ወላይታ ድቻ ወደ መሪዎቹ የቀረበበትን ድል አስመዝግቧል
ወልዋሎ ሰሞኑን ለተጫዋቾቹ ደሞዝ ሊከፍል ነው
ለባለውለተኞቻችን የተዘረጋው የሸዋረጋ ደስታ እና የጓደኞቹ ደጋግ እጆች
ሸገር ከተማ ተጨማሪ ተጫዋቾች አስፈርሟል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?