መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ “ከባህር ዳር ጋር በነበረን ጨዋታ እኛ ያገኘነውን እድል ስለተጠቀምን እነሱ ደግሞ ስላልተጠቀሙ አሸንፈናቸዋል”መስፍን ታፈሰ /ሐዋሳ ከተማ/
ሀዋሳ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

“ከባህር ዳር ጋር በነበረን ጨዋታ እኛ ያገኘነውን እድል ስለተጠቀምን እነሱ ደግሞ ስላልተጠቀሙ አሸንፈናቸዋል”መስፍን ታፈሰ /ሐዋሳ ከተማ/

አጋራ
አጋራ

የአሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረቱ ሐዋሳ ከተማ በጅማ ከተማ በሚገኘው የጅማ ዩንቨርስቲ ሜዳ ላይ ዛሬ ባደረገው የ7ተኛው ሳምንት የቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የሚመራውን ጠንካራውን ባህር ዳር ከተማን በመስፍን ታፈሰ እና በኤፍሬም አሻሞ ሁለት ግቦች 2-1 ሊያሸንፍ ችሏል። ለተጋጣሚው ደግሞ ምንም እንኳን ሽንፈትን ቢያስተነሠግዱም ሳህለወርቅ ተገኝ ነው አንዷን ግብ ሊያስቆጥር የቻለው።
ከሐዋሳ ከተማ እና ከባህር ዳር ከተማ ጨዋታ በኋላ የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ምን ይመስል እንደነበርና ስላገኙት ድል እንደዚሁም ደግሞ ስለ ወቅታዊ አቋማቸው እና ለቡድኑ ጎሎችን በማስቆጠር ስላለበት ሁኔታ ተጨዋቹ ከጋዜጠኛ መሸሻ ወልዴ /G.BOYS/ ጋር አጠር ያለ ቆይታን አድር ጓል፤ ተከታተሉት።

ስለ ዛሬው ጨዋታ እና ስለ ድላቸው

“ጨዋታው ደስ የሚል እና ጥሩ ፉክክር የተደረገበት ነበር። በሁለታችንም በኩል የጎል ዕድልንም ስንፈጥር ነበር። ያም ሆኖ ግን እኛ ያገኘነውን ዕድል በመጠቀማችንና እነሱ ደግሞ ሊጠቀሙ ስላልቻሉ አሸንፈናቸዋል። በውጤቱም በጅማ ከተማ ላይ ያገኘነው የመጀመሪያችን ድል ስለሆነ በጣም ተደስተናል”።

ስለ ዛሬ ተጋጣሚያቸው

“ባህር ዳር ጠንካራ እና ጥሩ ቡድን ነው። በጨዋታው ብዙ የግብ ዕድሎችን ፈጥረዋል። ሊጠቀሙበት አልቻሉም”።
ወደ አሸናፊነት መንፈሱ ስለመምጣት ሚስጥራቸው
“አንድነታችንና ህብረታችን ነው ለእዛ ያበቃን። ወደ ሜዳ ስንገባም የግድ ግጥሚያዎችን ማሸነፍ አለብን ብለን በቁርጠኝነት ስለምንገባም ፈጣሪ ረድቶን ጥሩ ውጤት እያስመዘገብን ይገኛል”።

ቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊጉ ሲጀመር ከውጤት ማጣታቸው ጋር ተያይዞ ሐዋሳ ሊወርድ ይችላል ስለመባሉ

“ሐዋሳ ከተማ በአዲስ አበባ ባደረገው የቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ የጅማሬ ጨዋታዎች ላይ ውጤቶችን ባጣበት ሰዓት እንዳልከው ስለ እኛ ብዙ ተብሎ እና ወራጅ ሊሆን ይችላልም በሚል ተነግሮ ነበር። ይሄን ስንሰማ ቡድናችንን ስለምናውቅ አንዳች ስጋት በእኛ ውስጥ አልነበረም። ሐዋሳ ሊጉ ሲጀመር ውጤትን ያጣው የአዲስ አበባ አየር ስለከበደው እና ከሜዳ ላይ እንቅስቃሴም አንፃር የራሳችን የሆኑ ችግሮች ስለነበሩብን እንጂ ለተጋጣሚዎቻችን እጃችንን ሰጥተን አልነበረምና ከእዛ በኋላ ባደረግነው ጨዋታ አቋማችንን እያስተካከልን በመምጣታችንና የአሰልጣኛችንንም ታክቲክ እየተገበርን በመምጣታችን በዛሬው ጨዋታ ደግሞ የጅማ ከተማ አየር ከአዲስ አበባው አየር ጥሩ ለመጫወት የረዳን በመሆኑ እነዚህ ወደ ውጤታማነት እንድንመጣ አድርጎናል”።

ለሐዋሳ ከተማ ጎሎችን ስለ ማስቆጠሩ እና ስለ ቀጣይ ጨዋታዎቻቸው

“አጥቂ እንደመሆኔ ቡድኔ ጎሎችን ከእኔ ይጠብቃል። ያን ስለማውቅም አሁን ላይ በየተሰለፍኩባቸው ጨዋታዎች ላይ ግቦችን ማስቆጠር ጀምሬያለሁ። ይሄ ቀጣይነትም የሚኖረው ነው። ለሐዋሳ ብዙ ጎሎችን የማስቆጠር እልም አለኝ። ይሄን ቡድን ከፈጣሪ እርዳታ ጋር ጥሩ ውጤት እንዲያስመዘግብም የሚቻለኝን ሁሉ አደርጋለሁ። በቀጣይ ጨዋታዎቻችንም ቡድናችን አሁን በያዘው የአሸናፊነት መንፈስ በመጓዝ ውጤታማም እንደሚሆን አምናለው”።

ስለ ቡድናቸው ስብስብ

“ወጣት ተጨዋቾች በብዛት አሉን። ልምድ ያላቸውንም ጥቂት ልጆች አካተናል። ሁሉንም እንደየተራው በማስገባት ቡድናችን እየተጠቀመባቸው ይገኛል”።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...