የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ በቀድሞው አሰልጣኙ ለመሰልጠን ሊያመራ ተቃርቧል።
በአሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት የሚመሩት መቻሎች በቀሩት የሊጉ ጨዋታዎች ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመገኘት ቡድናቸውን ማጠናከር የጀመሩት ሲሆን ባሏቸው ሦስት ቦታዎች የመጀመሪያ ተጫዋቻቸውን ለማስፈረም ከጫፍ እንደደረሱ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
ክለቡን ለመቀላቀል ዛሬ የህክምና ምርመራውን የሚያደርገው ደግሞ የአማካይ ተጫዋቹ ሳምሶን ጥላሁን (ሳሚ ባሪያው) ነው። የቀደምው በቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ኢትዮጵያ ቡና፣ ባህርዳር ከተማ፣ ሀዲያ ሆሳዕና እና ወልቂጤ ከተማ ተጫዋች በሀድያ ሆሳዕና ቆይታው ከአሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት ጋር አብሮ መስራቱም ይታወሳል።

አስተያየት ይስጡ