በአጋማሹ የመቻል ሁለተኛው አዲስ ተጫዋች ወጣቱ ተከላካይ ሆኗል።
ባለባቸው ክፍት ቦታዎች ውስጥ አዳዲስ ተጫዋቾችን ከዝውውሩ መዘጋት በፊት ወደ ቡድናቸው እየቀላቀሉ የሚገኙት መቻሎች ከሳምሶን ጥላሁን ቀጥሎ የአጋማሹ ሁለተኛው ፈራሚያቸው ወጣቱ ተከላካይ ሚያኪያስ ካሳሁን መሆኑን ለማረጋገጥ ችያለሁ።
ከቅዱስ ጊዮርጊስ ወጣት ቡድን ተነስቶ በመቀጠል ለትውልድ ከተማው ድሬዳዋ ከተማ እና ያለፉትን ሦስት አመታት ደግሞ ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ከከፍተኛ ሊጉ አንስቶ እስከ ፕሪምየር ሊጉ ድረስ በመጫወት ሲያገልግል ቆይቶ ከሳምንት በፊት ከኤሌክትሪክ ጋር መለያየቱን ነግረናችሁ ነበር። አሁን ደግሞ ተከላካዩ ወደ ሌላኛው የፕሪምየር ሊጉ ክለብ መቻል አምርቷል።
አስተያየት ይስጡ