በሊጉ ለዋንጫ ከሚጠበቁ ቡድኖች መካከል አንዱ የሆነው መቻል አይቮሪኮስታዊ ተከላካይ አስፈረመ።
በአሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረት የሚመራው መቻል ዘንድሮ በሊጉ ለዋንጫ ከሚጠበቁ ቡድኖች መካከል አንዱ ቢሆንም በእስከ አሁኑ የስምንት ሳምንታት ጉዞ ግን ውጤቶች የሰመረለት አይመስልም በቡድኑ ውስጥ ያለውን ችግር ለመቅረፍም ውል እያለው ወደ ሀገሩ ባመራው ጋናዊ ተከላካይ ምትክ ክለቡ ለማስፈረም ሲያደርግ የነበረው ጥረት ሰምሮ ረጅሙን አይቮሪኮስታዊ ተከላካይ ታውላ ቲዎፍሊንን እስከ አመቱ መጨረሻ ድረስ የግላቸው ማድረግ ችለዋል።
ለሀገሩ ክለቦች ዴንጉል ፣ አቢጃን እና አሴክ ሜሞሳ ከተጫወተ በኋላ ያለ ክለብ ተጫዋቹ ይገኝ ነበር።


