መነሻ ገጽ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ አቻ ተለያይተዋል
ሲዳማ ቡናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዳማ ከተማዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ አቻ ተለያይተዋል

አጋራ
አጋራ

ሲዳማ ቡና በአምስተኛ ሳምንት ጨዋታ ከተጠቀሙት ቋሚ 11 ዳዊት ተፈራን ብቻ በመቀየር ያስገቡ ሲሆን በአንፃሩ አዳማ ከተማዎች ከአዲስ አበባ ከተማ ጋር አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ከተጠቀሙት ቋሚ አሰላለፍ ዮሴፍ ዮሀንስ ፤ አሜ መሀመድ እና አብዲሳ ጀማልን ቀይረው በማስገባት ጨዋታቸውን ጀምረዋል ።

የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ግብ ለማስተናግድ 3 ደቂቃዎች ብቻ ነበር የፈጁበት ። ሀብታሙ ገዛኸኝ ከማዕዘን ያሻማውን ኳስ ተጠቅሞ ግርማ በቀለ ሲዳማ ቡናን መሪ ያደረገ ግብ አስቆጠረ ። ከግቧ መቆጠር በኋላ አዳማ ከተማዎች የጨዋታ ብልጫ በመውሰድ መጫወት ችለዋል በአንፃሩ ሲዳማ ቡናዎች በመልሶ ማጥቃት ለመጫወት ሙከራዎችን አድርገዋል ።

በፈጣን እንቅስቃሴ ወደ ግብ ሲደርሱ የነበሩር አዳማ ከተማዎች የግብ ዕድሎችን በመፍጠር ረገድ 23 ደቂቃዎችን ለመጠበቅ ተገደዋል ። በደቂቃው ላይ አማኑኤል ጎበና ከሳጥን ውጪ የመታውን ኳስ ወደ ግብ ሲሞክረው የግቡ ቋሚ መልሶበት ወዲያው ያገኘው አቡበከር ወንድሙ በድጋሚ ወደ ግብ ቢሞክረውም በተክለማርያም ሻንቆ በቀላሉ ተይዞበታል ። ጫና ማድረጋቸውን የቀጠሉት አዳማ ከተማዎች 32ኛ ደቂቃ ላይ አቻ የሚያደርጋቸውን ግን አገኙ ። ሚሊዮን ሰለሞን ከማዕዘን ምት ያሻማውን ኳስ አማኑኤል ጎበና በግንባር በመግጭት አስቆጠረ ። በቀሩት የመጀመሪያ አጋማሽ ደቂቃዎች ሲዳማ ቡና በተሻለ ወደ ግብ ቢያመሩም ተጨማሪ ግብ ሳያስቆጥሩ የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ ጨዋታው ቀዝቀዝ ብሎ የታየበት ነበር ። በሁለቱም በኩል በተወሰኑ አጋጣሚዎቾ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ የሚደረጉ ጥረቶች ቢታዩም የግብ ሙከራዎችን ግን በቀላሉ ማድረግ አልቻሉም ።

በጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ ግን ቀደም ብሎ ከነበረው የተሻለ እንቅስቃሴ በሜዳ ላይ የታየ ሲሆን ከሁለቱም በኩል የአሸናፊነቱን ግብ የሚያስቆጥር ተጫዋች ማግኘት ሳይቻል ጨዋታወሰ በአቻ ውጤት ተጠናቋል ።

ውጤቱን ተከትሎም ከጨዋታው በፊት በእኩል ስድስት ነጥብ ላይ የነበሩት ሁለቱ ክለቦች ነጥባቸውን ሰባት ሰባት አድርሰዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...