መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ | ሀድያ ሆሳዕና በፍሬዘር ካሳ ብቸኛ ግብ ኢትዮጵያ ቡናን ረቷል
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ሀድያ ሆሳዕና በፍሬዘር ካሳ ብቸኛ ግብ ኢትዮጵያ ቡናን ረቷል

አጋራ
አጋራ

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከሀድያ ሆሳዕና ያገናኘ ሲሆን ሁለቱም ከድል መልስ መገናኘታቸው ጨዋታውን ተጠባቂ ያደረገው ነበር ። በጨዋታውም ፍሬዘር ካሳ ባስቆጠረው ብቸኛ ግብ የሙሉጌታ ምህረት ልጆች አሸንፈው ወጥተዋል ።

ሁለቱም ክለቦች በስምንተኛው ሳምንት ድል ባደረጉባቸው ጨዋታዎች ከተጠቀሙት ቋሚ አሰላለፍ አንድ አንድ ቅያሪ አድርገው ወደ ጨዋታው ገብተዋል ። በኢትዮጵያ ቡና በኩል አቤል እንዳለ እንዲሁም በሀድያ ሆሳዕና በኩል ኡመድ ኡክሪ በቋሚ አሰላለፉ መካተት የቻሉ ተጫዋቾች ናቸው ።

 

ጨዋታው ከመጀመሩ ኢትዮጵያ ቡናዎች ለቀድሞ ተጫዋቻቸው እያሱ ታምሩ የፎቶ ስጦታ አበርከተውለታል ።
ጨዋታው በአመዛኙ በመሀል ክፍል ላይ ኳስ ስትንሸራሸር የቆየችበት ነበር ። ቡናማዎቹ በተለመደው ከኋላ መስመርቶ በመጫወት ወደ ፊት ለመሄድ ሲያደርጓቸው የነበሩ ጥረቶች በሀድያ ሆሳዕና ከፍተኛ ጫና ምክንያት እንዳሰቡት ለመጫወት እንዲቸገሩ አድርጓቸዋል ። በሀድያ ሆሳዕና በኩልም የሚገኙ ኳሶችን በፍጥነት ወደ ተጋጣሚ ክልል በመላክ ከፊት መስመር ባሉ ተጫዋቾች አማካይነት የግብ ዕድሎችን የሚፈጥሩበትን መንገድ ሲፈልጉ ቆይተዋል ።

ኢትዮጵያ ቡናም ሆነ ሀድያ ሆሳዕና የግብ ሙከራዎችን በማድረግ ግብ ጠባቂዎችን ማስጨነቅ አልቻሉም ነበር ። በኢትዮጵያ ቡና በኩል አቡበከር ናስርን ብቻ መሰረት ያደረጉ ኳሶች በማጥቃት መስመሩ ላይ በተደጋጋሚ መታየታቸው ተጫዋቹ በቀላሉ በተከላካዮች ዕይታ ውስጥ እንዲገባ እና እንደፈለገው ለመንቀሳቀስ እንዳይችል አድርጎታል ።

በ28ኛው ደቂቃ ላይ የኢትዮጵያ ቡናው ተከላካይ ቴዎድሮስ በቀለ ለሌኛው ተከላካይ አበበ ጥላሁን ለማቀበል ሲሞክር ኳሱ ሀብታሙ ታደሰ እግር ስር ቢገባም ሀብታሙ ኳሱን መቆጣጠር ሳይችል ቀርቶ ወቶበታል ። በተመሳሳይ ከሁለት ደቂቃዎች በኋላም አበበ ለሀይሌ ገብረትንሳይ ለማቀበል ሲሞክር ሀብታሙ አግኝቶ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ኳሱን በሚገፊበት ሰዓት በሰራው ስህተት ኳሱ አምልጦት ወደ ውጪ ወጥቷል ።

41ኛው ደቂቃ ላይ በኢትዮጵያ ቡና በኩል አስራት ቱንጆ ለአቡበከር ናስር በጥሩ ዕይታ ያቀበለው ኳስ አቡበከር ሳይደርስበት ቀርቶ በሶሆሆ ሜንሱ ተይዟል ።

በሁለተኛው አጋማሽ በተመሳሳይ እንቅሰቃሴ የቀጠለው ጨዋታ በተለይም በቡናማዎቹ በኩል ወደ ግብ ለመድረስ የነበሩ ጥረቶች ከሀድያ ሆሳዕና ተከላካዮች ማለፍ የቻሉ አልነበሩም ።

በ63ኛ ደቂቃ ላይ ሳምሶን ጥላሁን ከግራ መስመር በረጅሙ የመታውን የቅጣት ምት ፍሬዘር ካሳ በግንባር ገጭቶ በማስቆጠር ሀድያ ሆሳዕናን መሪ አደረገ ። ከግቡ በኋላ ጨዋታው ቀድሞ ከነበረው በተሻለ መነቃቃት የተካሄደ ሲሆን ሀድያ ሆሳዕናዎች በመከላከል ላይ አመዝነው ግቡን አስጠብቀው ለመውጣት ጥረቶችን ያደረጉበት ነበር ።

66ኛ ደቂቃ ላይ የሀድያ ሆሳዕና ተከላካዮች ኳስ ለማውጣት ሲሞክሩ ኳሱን ያገኘው አቤል እንዳለ የግብ ጠባቂውንም መውጣት ተመልክቶ ወደ ግብ የመታው ኳስ ለጥቂት ወደ ውጪ ወቶበታል ። 80ኛው ደቂቃ ላይም አቡበከር ናስር ከሮቤል ተክለሚካኤል የደረሰውን ኳስ በግሩም ሁኔታ በመቆጣጠር ወደ ሳጥን ይዞት የገባውን ኳስ ረዝሞበት ግብ ጠባቂው ሶሆሆ ሜንሱ ይዞታል ።

በ80ዎቹ ደቂቃዎች መገባደጃ ላይ ሀድያ ሆሳዕናዎች ባገኟቸው ክፍተቶች ተጠቅመው በፀጋዬ ብርሀኑ እና በሳምሶን ጥላሁን የፈጠሯቸው የግብ ዕድሎች በግብ ጠባቂው በረከት አማረ በቀላሉ ተይዘዋል ። ጨዋታውም በሀድያ ሆሳዕና 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቀቀ ።

ውጤቱን ተከትሎም ሀድያ ሆሳዕና ነጥቡን 12 በማድረስ ደረጃውን ወደ 7ኛ ሲያሻሽል ኢትዮጵያ ቡና በ14 ነጥብ ባለበት 4ኛ ደረጃ ላይ ቆይቷል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

ገዛኸኝ ደሳለኝ (ሸገር ከተማ) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ባደረገው የ26ኛ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...