መነሻ ገጽ ሀዋሳ ከተማ የጨዋታ ዘገባ | ከእረፍት በፊት በተቆጠሩ ግቦች አዲስ አበባ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
ሀዋሳ ከተማቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዲስአበባ ከተማዜናዎችየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ከእረፍት በፊት በተቆጠሩ ግቦች አዲስ አበባ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

አጋራ
አጋራ

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ የተገናኙት አዲስ አበባ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማ ተመጣጣኝ እና ጥሩ ፉክክር አድርገው ከእረፍት በፊት ባስቆጠሯቸው አንድ አንድ ግቦች አቻ ሊለያዩ ችለዋል ።

አዲስ አበባ ከተማ በሰባተኛው ሳምንት ጨዋታ በወልቂጤ ከተማ በተሸነፉበት ጨዋታ ከነበረው ቋሚ አሰላለፍ ሶስት ቅያሪዎችን በማድረግ ዋኬኔ አዱኛ ፤ ዘሪሁን አንሼቦን እና ሙሉቀን አዲሱን ማሰለፍ የቻሉ ሲሆን በሀዋሳ ከተማ በኩል ሰበታ ከተማን ባሸነፉበት ጨዋታ ከተጠቀሙት ቋሚ አስራአንድ አንድ ቅያሪ ብቻ በማድረግ መድኃኔ ብርሀኔ ጨዋታውን እንዲጀምር አድርገዋል ።

በጨዋታው ጅማሮ የሀዋሳ ከተማዎች በፍጥነት ወደ ግብ የመድረስ ፍላጎት የታየበት ነበር ። ቀስ በቀስም ወደ ጨዋታው የተመለሱት አዲስ አበባ ከተማዎች ረጅም ኳሶችን እና በመስመር ላይ ባሉት እንዳለ ከበደ እና ፍፁም ጥላሁን አማካኝነት ለአጥቂው ኦዶንጎ በሚደላኩ ኳሶች ግቦችን ለማግኘት የጣሩበት ነበር ።

የሁለቱም ቡድኖች ፈጣን እንቅስቃሴ በጥሩ ፉክክር ቢቀጥልም የግብ ሙከራዎችን በማድረግ ረገድ ግን እምብዛም ነበር ። ሀዋሳ ከተማ በመስፍን ታፈሰ እና ብሩክ በየነ የግብ ዕድሎችን ለመፍጠር ያደረጉት ሙከራ ኢላማቸውን ሳይጠብቁላቸው ወደ ውጪ ወተዋል ።

35ኛ ደቂቃ ላይ በፈጣን መልሶ ማጥቃት ከግብ ክልላቸው ኳስ ነጥቀው የወጡት አዲስ አበባ ከተማዎች በተጠቀሰው ደቂቃ መሪ መሆን የቻሉበትን ግብ አግኝተዋል ። በግራ መስመር ላይ የነበረው እንዳለ ከበደ ከሙሉቀን አዲሱ የደረሰውን ኳስ በሳጥን ውስጥ ሮጦ ለገባው ረችሞንድ ኦዶንጎ በአየር ላይ አድርሶት አጥቂው በግሩም ሁኔታ በግንባር በመግጨት አስቆጥሮታል ።

ግቧ ከተቆጠረች በኋላ ሀዋሳ ከተማዎች ግብ ለማግኘት የወሰደባቸው ሶስት ያህል ደቂቃዎች ብቻ ነበር ። ወንድማገኝ ሀይሉ ፤ ብሩክ በየነ እና መስፍን ታፈሰ ያደረጉት ጥሩ ቅብብል ለኤፍሬም አሻሞ ደርሶት ኤፍሩም በጥሩ አጨራረስ ሀዋሳ ከተማን አቻ ያደረገ ግብ አስቆጠረ ። በቀጣዮቹ የመጀመሪያ አጋማሽ መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ አዲስ አበባ ከተማዎች ከቆሙ ኳሶች የፈጠሯቸው የግብ ዕድሎች በግብ ጠባቂው በመመለስ እና ወደ ውጪ በመውጣት ግብ ሳይሆኑ ቀርተዋል ።

በሁለተኛውም አጋማሽ ልክ እንደመጀመሪያው አጋማሽ ሁሉ በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጥሩ ፉክክር የታየበት ነበር ምንም እንኳን በቀላሉ የግብ ዕድሎች ያልታየበት ጨዋታ ቢሆንም ።

58ኛው ደቂቃ ላይ ኤፍሬም አሻሞ ከክንፍ ወደ ግብ ሳጥን ውስጥ ያሻገረው ኳስ መስፍን ታፈሰ ለጥቂት አመለጠችው እንጂ ሀዋሳ ከተማ መሪ መሆን የሚችልበት ትልቅ ዕድል ነበር ። እስከ 80ዎቹ መጨረሻዎች ወደ ተጋጣሚያቸውን የግብ ክልል በመድረስ የግብ ሙከራ ለማድረግ አይናፋር የሆኑት አዲስ አበባ ከተማ እና ሀዋሳ ከተማዎች በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ በተመሳሳይ መንገድ በተባረክ ሄፌሞ ( ሀዋሳ ከተማ ) እና ፍፁም ጥላሁን ( አዲስ አበባ ከተማ ) አማካኝነት ለግብ የቀረቡ ዕድሎችን ማግኘት ቢችሉም ሳይሳካላቸው ቀርቷል ።

ውጤቱን ተከትሎም በእኩል 10 ነጥብ ላይ የነበሩት ሁለቱ ክለቦች አንድ አንድ ነጥብ በመጨመር በእኩል 11 ነጥብ በግብ ክፍያ ተበላልጠው 6ኛ ( ሀዋሳ ከተማ ) እና 7ኛ ( አዲስ አበባ ከተማ ) ደረጃ ላይ መቀመጥ ችለዋል ።

 

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...