መነሻ ገጽ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ የውድድር አመቱን የመጀመሪያ ሽንፈት አስተናግደዋል
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግአዲስአበባ ከተማዜናዎችየጨዋታ ዘገባፋሲል ከነማ

የጨዋታ ዘገባ | አፄዎቹ በአዲስ አበባ ከተማ የውድድር አመቱን የመጀመሪያ ሽንፈት አስተናግደዋል

አጋራ
አጋራ

በአራተኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን የመጀመሪያ ጨዋታ ሊጉን ከሶስት ሶስት በማሸነፍ በመምራት ላይ የነበረው ፋሲል ከነማ በመነቃቃት ላይ ባለው አዲስ አበባ ከተማ 2 ለ 1 ተሽንፏል ።

በጨዋታው ፋሲል ከተማዎች በሙሉ ደቂቃው ደክመው የተሴተዋሉ ሲሆን በአንፃሩ ከሁለት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ መከላከያን በማሸነፍ የተነቃቁት አዲስ አበባ ከተማዎች የተጋጣሚያቸውን አጨዋወት በመግታተ ያሰቡትን አሳክተው ለመውጣት ችለዋል ።

በጨዋታው የመጀመሪያ ሙከራ ማድረግ የቻሉት አዲስ አበባ ከተማዎች ሲሆኑ አምስተኛ ደቂቃ ላይ በሪችሞንድ ኦዶንግ አማካኝነት ኢላማውኔ የጠበቀ ሙከራ ቢያደርጉም በሚካኤል ሳማኪ ተመልሷል ። ፋሲል ከተማዎች ኳስን ይዘው ለመጫወት ቢሞክሩም ወደ ፊት በሚሄዱበት ጊዜ የነበራቸው ድክመት የግብ ሙከራዎች በቀላሉ እንዳያደርጉ አድርጓቸዋል ።

አዲስ አበባ ከተማዎች በፋሲል ከተማ ተከላካዮች ስህተት ግብ የማስቆጠር አጋጣሚን ማግኘት ቢችሉም ኦዶንግ የመታው ኳስ በሳማኪ ተመልሶ የማዕዘን ምት ሆኗል ።

በጨዋታው 20ኛ ደቂቃ ላይ አዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ግብ ማስቆጠር ቻሉ ። ከመስመር የተሻማውን ኳስ ሳማኪ በእግሩ ለመመለስ ሲሞክር ኳሱ አልፎት የአዲስ አበባ ከተማው አጥቂ ኦዶንጎ በግንባር በመግጨት አስቆጠረ ።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ አዲስ አበባ ከተማዎች ከመስመር በተነሳ ኳስ ግብ የማስቆጠር ዕድልን በፍፁም አማካኝነት አግኝተው የነበረ ቢሆንም በድጋሚ በሳማኪ ሊመለስ ችሏል ።

አፄዎቹ የነበራቸው እንቅስቃሴ ወደ ግብ በመድረስ ረገድ ክፍተቶች የነበሩት ሲሆን በዚህ ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ተከላካዮች በኩል የነበረው ጥረት የሚደነቅ ነበር ።

በ39ኛው ደቂቃ ላይ ከግብ አስቆጣሪው ኦዶንግ በሳጥን ውስጥ የደረሰውን ኳስ ተጠቅሞ ኤልያስ አህመድ የአዲስ አበባን ከተማን ሁለተኛ ግብ አስቆጠረ ።

የጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽም በአዲስ አበባ ከተማ የ2 ለ 0 መሪነት ተጠናቀቀ ።

በሁለተኛው አጋማሽ በአፄዎቹ በኩል ግቦችን ለማስቆጠር በተለያዩ አቅጣጫዎች ጥረቶችን ሲያደርጉ የተስተዋለ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ በኩል ደግሞ በመከላከሉ ጠንክረው በመግባት ውጤቱን አስጠብቀው ለመውጣት ሞክረዋል ።

በተደጋጋሚ ወደ ግብ ቢሄዱም የአዲስ አበባ ተከላካይ መስመርን ሰብረው ለመግባት የተቸገሩት ፋሲል ከተማዎች 62ኛ ደቂቃ ላይ ግብ አስቆጠሩ ። ከቀኝ መስመር የተሻገረውን ኳስ ፍቃዱ አለሙ በግንባር በመግጨት አስቆጠረ ።

ከግቧ መቆጠር በኋላ አፄዎቹ ተጨማሪ ግብ ለማስቆጠር ጥረቶችን ማድረግ ቢችሉም ኳሷን ከመረብ የሚያዋህድ ተጫዋች ማግኘት አልቻሉም ። አዲስ አበባ ከተማዎችም በጠንካራ መከላከል ጨዋታውን በአሸናፊነት አጠናቀው መውጣት ችለዋል ።

በዚህም አዲስ አበባ ከተማ ነጥቡን ወደ ስድስት ሲያሳድግ ፋሲል ከተማ ባለበት ዘጠኝ ነጥብ ለመቆየት ተገደዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

አዳማ ከአስር ፈረሰኞቹ ከሦስት እና ነብሮቹ ከአራት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

በሊጉ የሳምንቱ የመክፈቻ ቀን ጨዋታ አዳማ ከተማ በጎል ደምቆ ሲያሸንፍ ቅዱስ ጊዮርጊስ...

ዜናዎችየአዲስአበባ እግርኳስ ፌዴሬሽንየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ውጤት ለውጠዋል የተባሉት ሁለት ዳኞች ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደረገ

በዮሴፍ ከፈለኝ በወልዋሎ እና ነገሌ አርሲ ጨዋታ ላይ ውጤት ለውጠዋል የተባሉ ሁለት...

ቅዱስ ጊዮርጊስዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንፊፋ

ፊፋ ቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ ጥሎት የነበረውን የዝውውር ዕገዳ በጊዜያዊነት አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በአራት የቀድሞ ተጫዋቾች ቀርቦበት በነበረው ክስ በፊፋ ጥሎበት የነበረው የተጫዋቾች...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

ዋልያዎቹ በአሜሪካ የወዳጅነት ጨዋታን ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ሊያመራ ነው ነገር ግን የወቅቱ የብሔራዊ ቡድኑ...