By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ባህርዳር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን በሰፊ ውጤት ሲረታ መቻል እና ድሬዳዋ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስድሬዳዋ ከተማባህርዳር ከተማየጨዋታ ዘገባመቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ባህርዳር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን በሰፊ ውጤት ሲረታ መቻል እና ድሬዳዋ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ20ኛ ሳምንት የመጨረሻ ቀን መርሐግብሮች አስቀድመው 129ኛውን የዓድዋ ድል በዓልን በመዘከር ተደርገዋል።

በዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ የተገናኙት መቻል እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታቸውን ያለ ግብ በማጠናቀቅ ከድል ጋር እንደተራራቁ ቀጥለዋል።

በጨዋታው መቻሎች የተሻለ የኳስ ቁጥጥር እና የግብ ዕድል መፍጠር ቢችሉም ኳስ እና መረብን ማገናኘት ሳይችሉ ቀርተዋል።

የአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራው ቡድን የዛሬውን ጨምሮ ባለፉት ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም።

- ማሰታውቂያ -

በተጨማሪም ቡድኑ ካለፉት ዘጠኝ ጨዋታዎች በአንዱ ብቻ ያሸነፈ ሲሆን በሶስት ተከታታይ የሊጉ ጨዋታዎችም ግብ ማስቆጠር አልቻለም።

ድሬዳዋ ከተማ በበኩሉ ተከታታይ ዘጠነኛ ድል አልባ የሊግ ጨዋታውን አድርጓል።

በአስረኛው ሳምንት ሳምንት ሲዳማ ቡናን ካሸነፈ በኋላ ሶስት ነጥብ ማሳካት ያልቻለው ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት ሰባት የሊጉ ጨዋታዎች ማስቆጠር የቻለው ሁለት ግቦችን ብቻ ነው።

ውጤቱን ተከትሎ መቻል ነጥቡን 28 ሲያደርስ ድሬዳዋ ከተማ በበኩሉ ነጥቡን 21 አድርሷል።

በ21ኛው ሳምንት መርሐግብር መቻል ከወልዋሎ አዲግራት ሲገናኝ ድሬዳዋ ከተማ በበኩሉ የሊጉን መሪ ኢትዮጵያ መድንን ይገጥማል።

በሳምንቱ የመጨረሻ እና በዕለቱ ሁለተኛ መርሐግብር አስቀድሞ ግብ አስቆጥሮ ይመራ የነበረው ቅዱስ ጊዮርጊስ በባህርዳር ከተማ 4 ለ 1 ተረቷል።

በጨዋታው 14ኛ ደቂቃ ላይ ተገኑ ተሾመ ከቢንያም ፍቅሬ የደረሰውን ኳስ ተጠቅሞ ፈረሰኞቹን መሪ ማድረግ ችሎ ነበር።

ግብ ካስተናገዱ በኋላ ከቆሙ ኳሶች በተለይም ደጋግመው ካገኟቸው የማዕዘን ምቶች ቅዱስ ጊዮርጊስን የፈተኑት ባህርዳር ከተማዎች በ39ኛው ደቂቃ ላይ አቻ ሆነዋል።

መሳይ አገኘሁ ከርቀት የተገኘውን የቅጣት ምት በቀጥታ ወደ ግብ ልኮት በቅዱስ ጊዮርጊስ መረብ ላይ አርፏል።

ከዕረፍት መልስ ደግሞ በ61ኛው ደቂቃ ላይ ከማዕዘን ምት የተሻገረን ኳስ ወንደሰን በለጠ አስቆጥሮ ቡድኑን መሪ አድርጓል።

ሁለተኛውን የባህርዳር ከተማ ግብን ያስቆጠረው ወንደሰን በለጠ የቅዱስ ጊዮርጊስ ተከላካዮችን መዘናጋት እና የባህሩ ነጋሽን ትክክል ያልነበሩ ቦታ አያያዞችን በመጠቀም በ83 እና 85ኛ ደቂቃዎች ላይ ሁለት ግቦችን አስቆጥሮ ሀትሪክ በመስራት ቡድኑ 4 ለ 1 እንዲያሸንፍ አስችሏል።

ወንደሰን በለጠ በ2017 ዓመተ ምህረት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሀትሪክ የሰራ ቀዳሚው ተጫዋችም ሆኗል።

ውጤቱን ተከትሎ ባህርዳር ከተማ ነጥቡን 29 በማድረስ ወደ 3ኛ ደረጃ ከፍ ሲል ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ 5ኛ ደረጃ ዝቅ ብሏል።

በቀጣይ ሳምንት መርሐግብር ባህርዳር ከተማ ከፋሲል ከተማ እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከወላይታ ድቻ ይገናኛሉ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጦና ንቦቹ የሊጉን መሪ ሲረቱ አዞዎቹ አፄዎቹን በድጋሚ አሸንፈዋል
Next Article የሃያኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorizedየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንዜናዎችLIVESCORE

የ2022 የኳታር አለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታ/LIVESCORE/

Fitsum Nigusse By Fitsum Nigusse 7 years ago
ቢንያም ፍቅሬ የ31 ጊዜ ሻምፒዮኖቹን ተቀላቅሏል
ኦሎምፒክ ማጣሪያ | ኢትዮጵያ ከ ሶማሊያ በቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/ ይከታተሉ
“በእርግጠኝነት ሻምፒዮን እንሆናለን” “ዘሪሁን ጥያቄውን እንዳቀረብልኝ አላንገራገርኩም” “ጊዮርጊስ ቤት አቻ ሽንፈት ነው” አማኑኤል ኤርቦ
ፋሲል ከነማና አሰልጣኝ ሃይሉ ነጋሽ መለያየታቸው ርግጥ ሆኗል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?