By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ነፃነት ክብሬ ለተከታታይ አራተኛ ጨዋታ ዘርዓይ ሙሉን አሸንፏል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችሀዋሳ ከተማየጨዋታ ዘገባ

ነፃነት ክብሬ ለተከታታይ አራተኛ ጨዋታ ዘርዓይ ሙሉን አሸንፏል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በፕሪሚየር ሊጉ የሶስተኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀን ቀዳሚ መርሐግብር ኢትዮጵያ ቡና ሀዋሳ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል።

የአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬው ቡድን ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ነጥብ ከተጋራው ቡድን ምርጥ 11 አንድ ለውጥ ብቻ በማድረግ ይታገሱ ታሪኩን በስንታየሁ ዋለጬ ተክተው ጨዋታውን ሲጀምሩ በሀዋሳ ከተማ በኩል ደግሞ ከስሁል ሽረ ነጥብ ከተጋራው ቡድን የመጀመሪያ አሰላለፍ አራት ለውጦችን በማድረግ ፀጋአብ ዮሐንስ ፣ ወንድማገኝ ማዕረግ ፣ ግርማ በቀለ እና ቢንያም በላይ በበረከት ሳሙኤል ፣ ሰለሞን ወዴሳ ፣ አቤኔዘር ዮሐንስ እና ተባረክ ሄፋሞ ተተክተው ጨዋታውን ጀምረዋል።

በጨዋታው ቀዳሚ ደቂቃዎች ላይ ሀዋሳ ከተማ ኳሱን በማንሸራሸር በተለይም በመስመሮች በኩል በግራ መስመር ባደላ መልኩ በተደጋጋሚ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ጥረቶችን አድርገዋል።

በኢትዮጵያ ቡና በኩል በፈጣን እና በቁጥር አነስተኛ በሆኑ የኳስ ቅብብሎች በሀዋሳ ከተማ የግብ ክልል በተደጋጋሚ በመድረስ የተሻሉ የግብ ዕድሎችን ፈጥረዋል።

- ማሰታውቂያ -

የጨዋታው ቀዳሚ የግብ ሙከራ በኢትዮጵያ ቡና በኩል ሲደረግ አምበሉ ራምኬል ጀምስ በጨዋታው ጅማሮ ሰከንዶች ውስጥ ከማዕዘን የተሻገረን ኳስ በግንባር ገጭቶ ወደ ግብ ሞክሮ ኳሱ ኢላማውን ሳይጠብቅ ቀርቷል።

በሶስተኛው ደቂቃ ላይ ሀዋሳ ከተማዎች በፈጣን እንቅስቃሴ ወደ ኢትዮጵያ ቡና ሳጥን ይዘው የገቡትን ኳስ ሳይጠቀሙበት ቀርተዋል። በአጋጣሚው አሊ ሱሌማን እየገፋ ይዞ የገባውን ኳስ በግብ ጠባቂው ተጨርፎ ሲመለስ ኳሱን በቅርበት ያገኘው ግርማ በቀለ አልጠቀመበትም።

ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሀዋሳ ከተማዎችን የኳስ ምስረታ ስህትት ተጠቅሞ በሳጥኑ ውስጥ ከግብ ጠባቂው ጋር ፊት ለፊት የተገናኘው አንተነህ ተፈራ በማይታመን መልኩ ኳሱን ከግቡ አናት በላይ ልኮታል።

ጨዋታው 24ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ ቀዳሚው ግብ ተቆጥሯል። በፍቃዱ አለማየሁ ከሳጥን ውጪ ወደ ግብ ሞክሮ በተከላካዮች ተደርቦ በሳጥን ውስጥ የቀረውን ኳስ ወንድማገኝ ሀይሉ በተገቢው መልኩ ከግቡ ለማራቅ ሲቸገር የደረሰበት ኮንኮኒ ሁዛፍ ኳስና መረብን አገናኝቷል።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላም በፍቃዱ አለማየሁ ከርቀት አክርሮ የመታው ኳስ የግቡን አግዳሚ ለትሞ ተመልሷል።

በሀዋሳ ከተማ በኩል በተደጋጋሚ በተለይም በቢንያም በላይ አማካይነት ሲደረጉ የነበሩ ተደጋጋሚ ጥረቶች ጠንካራ አደረጃጀት በነበረው የኢትዮጵያ ቡና የተከላካይ ክፍል በቀላሉ ሲበላሽ ቆይቷል።

ከግቡ በኋላ በይበልጥ ጨዋታውን ተቆጣጣሮ የቀጠለው ኢትዮጵያ ቡና ውጤቱን አስጠብቆ የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ገና ከጅማሮው ቶሎ ቶሎ ወደ ኢትዮጵያ ቡና ሳጥን መድረስ የቻለው ሀዋሳ ከተማ በ47ኛው ደቂቃ ላይ አቻ የሆነበትን ግብ አግኝቷል።

ከቀኝ መስመር የተሻገረውን ኳስ እስራኤል እሸቱ ለአሊ ሱሌማን አቀብሎት የ2016 የሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ አሊ ሱሌማን ኳስና መረብን አገናኝቷል።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ በሁለቱም በኩል አስቀድሞ ሁለተኛውን ግብ ለማስቆጠር ጥረቶች ሲደረጉ የቡናማዎቹ የማጥቃት እንቅስቃሴ ከተጋጣሚያቸው የተሻለ ነበር። ነገር ግን ሙከራዎቻቸው ያን ያህል ሰይድ ሀብታሙን የፈተኑ አልነበሩም።

76ኛው ደቂቃ ላይ ግን ራምኬል ጀምስ ከበፍቃዱ አለማየሁ የተሻገረለትን የማዕዘን ኳስ ነፅ ሆኖ በማግኘት ኳስና መረብን አገናኝቷል።

ከሶሰት ደቂቃዎች በኋላም ዳግም የሀዋሳ ከተማ የተከላካይ መስመር ስስነት በታየበት አጋጣሚ ተቀይሮ የገባው ዳዊት ሽፈራው የኢትዮጵያ ቡናን 3ኛ ግብ አስቆጠሯል።

በመጨረሻም ቡናማዎቹ የውድድር ዓመቱ ቀዳሚ ድላቸውን ነጥባቸውንም አራት ያደረሱበትን ውጤት አስመዝግበው ወጥተዋል።

ኢትዮጵያ ቡናን ከያዘ በኋላ በፕሪሚየር ሊግ እና በኢትዮጵያ ዋንጫ ሀዋሳ ከተማን በአራት ጨዋታዎች የገጠመው ነፃነት ክብሬ በአራቱም ማሸነፍ ችሏል።

በአራተኛ ሳምንት ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና ከወላይታ ድቻ እንዲሁም ሀዋሳ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ፋሲል ከነማ እና ስሑል ሽረ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል
Next Article የአትሌቲክስ ስፖርት ባለውለታዎችን ለማስታረቅ የተደረገው ጥረት ከሸፈ…

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችሀዋሳ ከተማ

የጨዋታ ዘገባ | የተባረክ ሄፋሞ ብቸኛ ግብ ሀዋሳ ከተማን የደርቢው አሸናፊ አድርጓል

Habtamu Mitku By Habtamu Mitku 1 year ago
የ2015 ሶፊ ማልት ሀዋሳ ግማሽ ማራቶን ላይ ለሚሳተፉ አትሌቶች ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል።
የዋልያዎቹ አሰላለፍ ይፋ ሆናል
ፋሲል ከነማ የመስመር አጥቂ አስፈርሟል !!
አቶ ኢሳያስ ጅራ በሴካፋ ምክትል ፕሬዝዳንትነት በድጋሚ ተመረጡ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?