By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የተባረክ ሄፋሞ ብቸኛ ግብ ሀዋሳ ከተማን የደርቢው አሸናፊ አድርጓል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችሀዋሳ ከተማሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | የተባረክ ሄፋሞ ብቸኛ ግብ ሀዋሳ ከተማን የደርቢው አሸናፊ አድርጓል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታ መቀመጫቻውን በሀዋሳ ከተማ ያደረጉት ሲዳማ ቡናን ከሀዋሳ ከተማ አገናኝቶ በሀዋሳ ከተማ የ1 – 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ ሲዳማ ቡናዎች በኳስ ቁጥጥር የተሻሉ ሆነው በተጋጣሚ ሜዳ ላይ አብዛኛውን የጨዋታ አጋማሽ ማሳለፍ ችለዋል። በተጨማሪም ተደጋጋሚ የግብ ዕድሎችን ከመፍጠርም አንፃር ከሀዋሳ ከተማ የተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ችለዋል።

በሀዋሳ ከተማ በኩል በይበልጥ ከኳስ ውጪ ሆነው የጨዋታውን ክፍለ ጊዜ ሲያሳልፉ በሚነጠቁ ኳሶች በፈጣን ወደ ፊት በመድረስ የሲዳማ ቡናን የኋላ መስመር ለመፈተን ሞክረዋል።

የሲዳማ ቡና አብዛኛው የማጥቃት እንቅስቃሴ በነበረበት የቀኝ መስመር በተለይም ከብርሀኑ በቀለ እና ሬድዋን ናስር በሚጣሉ ኳሶች አሊቶዎቹ ዕድሎችን ፈጥረዋል።

- ማሰታውቂያ -

በ10ኛው ደቂቃ ከሳጥን ውጪ የግብ ሙከራ አድርጎ የነበረው መስፍን ታፈሰ ከሰከንዶች በኋላ ከቀኝ መስመር የተሻገረለትን ኳስ በግንባር ገጭቶ በተመሳሳይ ኢላማውን ሳይጠብቅለት ቀርቷል።

አበባየሁ ሀጂሶ በ13ኛው እንዲሁም መስፍን ታፈሰ በ27ኛው ደቂቃ ላይ ያደረጓቸው ኢላማቸውን የጠበቁ የግብ ሙከራዎች ግብ ጠባቂውን ሰይድ ሀብታሙን የፈተኑ አልነበሩም።

በጨዋታው 20ኛ ደቂቃ ላይ በሀዋሳ ከተማ በኩል የቀኝ መስመር ተከላካዩ እንየው ካሳሁን ጉዳት ማስተናገዱን ተከትሎ በሲሳይ ጋቾ ተቀይሮ ወጥቷል።

በ34ኛው ደቂቃ ላይ የሲዳማ ቡናው አምበል ያሬድ ባየህ ወደ ፊት ገፍቶ በመምጣት ወደ ሳጥን ያሻገረውን ኳስ በረከት ሳሙኤል በግንባር ገጭቶ ወደ ራሱ መረብ ልኮት የነበረ ቢሆንም ግቡን ለቆ ወቶ የነበረው ሰይድ ሀብታሙ ተቆጣጥሮታል።

የሲዳማ ቡናን የማጥቃት ሂደት በማቋረጥ ተጠምደው የቆዩትና የተጋጣሚያቸውን የሲዳማ ቡና የተከላካይ መስመር መፈተን ያልቻሉት ሀይቆቹ በ42ኛው ደቂቃ ላይ በመጀመሪያ ሙከራቸው ግብ አስቆጥረዋል።

እስራኤል እሸቱ በቀኝ መስመር ይዞ የሄደውን ኳስ በጥሩ ዕይታ ለተባረክ ሔፋሞ አቀብሎት ተባረክ ሔፋሞ ኳሱን ከመረብ አሳርፎታል።

በዚህ ግብም ሀዋሳ ከተማ የመጀመሪያውን አጋማሽ በመሪነት አጠናቋል።

በሁለተኛው አጋማሽ ሲዳማ ቡና ጫና ፈጥሮ የአቻነቱን ግብ ፍለጋ ሲጥሩ እስከመጨረሻው የዳኛው የጨዋታ ማገባደጃ የፊሽካ ድምፅ ድረስ ቆይተዋል።

በአንፃሩ ሀዋሳ ከተማዎች በመጀመሪያው አጋማሽ ያስቆጠሩትን ግብ አስጠብቀው ለመውጣት በሚመስል መልኩ ሙሉ ለሙሉ የግብ ክልላቸውን ሲከላከሉ ቆይተዋል።

የአጋማሹ ቀዳሚ የግብ ሙከራ በ58ኛው ደቂቃ ሲደረግ መስፍን ታፈሰ ወደ ግብ ያሻገረው ኳስ በአብዱልባሲጥ ከማል ተጨርፎ ሀብታሙ ታደሰ አግኝቶ በግንባር በመግጨት ወደ ግብ ሞክሮ ሰይድ እና የግቡ ቋሚ ኳሱን መረብ ላይ ከማረፍ አግደውታል።

በ67ኛው ደቂቃ ላይም መስፍን ታፈሰ ከአበባየሁ ሀጂሶ የተቀበለውን ኳስ ከሳጥኑ መግቢያ ሆኖ ግሩም ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ሰይድ ሀብታሙ በግሩም ብቃት ግብ እንዳይሆን አድርጎታል።

በሀዋሳ ከተማ በኩል በተለይም የመጨረሻ 15 ደቂቃዎች ላይ አጥቂው አሊ ሱሌማን ተደጋጋሚ ኳሶችን ቢያገኝም ኳሱን የሚያገኝበት ቦታ ከግቡ ያለው ርቀት እና አጋዥ ተጫዋች በማጣት ተደጋጋሚ ኳሶች ተበላሽተውበታል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቆ የተጨመሩት አምስት ደቂቃዎች ሊጠናቀቁ ሰከንዶች በቀሩበት ወቅት ይገዙ ቦጋለ በግራ መስመር ወደ ሳጥን ይዞ የገባውን ኳስ ቀንሶ ለኪፕሩቭ ለማቀበል ሲሞክር በረከት ሳሙኤል ኳሱን ተከላክሏል።

በመጨረሻም ሀዋሳ ከተማ በ1 – 0 ውጤት የጨዋታው አሸናፊ ሆኖ አጠናቋል።

በሁለተኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው መስከረም 17(አርብ) ረፋድ 3:30 ሀዋሳ ከተማ ከስሁል ሽረ እንዲሁም መስከረም 18(ቅዳሜ) 10:00 ሲዳማ ቡና ከመቻል ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ካርሎስ ዳምጠው አስደናቂ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ ወላይታ ድቻ አሸንፏል
Next Article የ2017 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔ!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎችዜናዎችአርባምንጭ ከተማ

ፍቃዱ አለሙ የአዞዎቹ አዲሱ ፈራሚ ሆኗል

ቴዎድሮስ ታከለ By ቴዎድሮስ ታከለ 1 week ago
ቅድመ ጨዋታ ዕይታ| ወልቂጤ ከ ባህርዳር ከተማ
የአሰልጣኞች አስተያየት | አዳማ ከተማ 3-0 ኢትዮጵያ ቡና
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከመመራት ተነስቶ ማሸነፍ ሲችል ፤ በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ የተከወነዉ የምሽቱ ጨዋታም በአቻ ዉጤት ፍፃሜዉን አጊኝቷል !!
አዲሶቹ የዳኞች ኮሚቴ ተመረጡ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?