By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ካርሎስ ዳምጠው አስደናቂ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ ወላይታ ድቻ አሸንፏል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችኢትዮ-ኤሌክትሪክየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ካርሎስ ዳምጠው አስደናቂ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ ወላይታ ድቻ አሸንፏል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በሊጉ የአንደኛ ሳምንት የሶስተኛ ቀዳሚ ጨዋታ ወላይታ ድቻ ኢትዮ ኤሌክትሪክን በሶስቱ አዲስ ፈራሚዎቹ ግቦች 3 – 1 አሸንፏል።

በመጀመሪያ አጋማሽ በሁለቱም በኩል ክፍት የጨዋታ እንቅስቃሴ የነበረ ሲሆን ጠንከር ያሉ ተደጋጋሚ የግብ ሙከራዎችን ከማድረግ አንፃር ግን እምብዛም ነበር።

በተደጋጋሚ ከተስተዋሉ የሚቆራረጡ ኳሶች በኋላ በ29ኛው ደቂቃ ላይ ፍቃዱ አለሙ ከሽመክት ጉግሳ የደረሰውን ኳስ ከሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ አግኝቶ ወደ ግብ ቢልከውም በቀላሉ በግብ ጠባቂው ተይዟል።

ከጥቂት ሰከንዶች በኋላ የሽመክት እና ፍቃዱ ጥምረት ሲደግም ናትናኤል ናሴሮ ደርሶ ሙከራውን ተከላክሏል።

- ማሰታውቂያ -

ጨዋታው 33ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ የጦና ንቦቹ መሪ መሆን ችለዋል። ያሬድ ዳርዛ ከአብነት ደምሴ የደረሰውን ኳስ ከመስመር ወደ ሳጥን በመግባት ለካርሎስ ዳምጠው ለማቀበል ሲሞክር ጌታሁን ባፋ በራሱ መረብ ላይ አሳርፎታል።

በቀጣዩቹ ደቂቃዎች ላይ ወላይታ ድቻዎች በተለይም ለግቡ መቆጠር መንስኤ በነበረው ያሬድ ዳርዛ አማካኝነት ተጨማሪ እድሎችን ለመፍጠር ጥረዋል።

በሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታው መሪዎች ወላይታ ድቻዎች ከተጋጣሚያቸው በተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴ አጋማሹን ጀምረዋል።

አጋማሹ በተጀመረ ሁለተኛው ደቂቃ ላይ ያሬድ ዳርዛ ከቀኝ መስመር ያቀበለው ኳስ በብሰራት መለሰ እና ብዙአየሁ ሰይፈ አልፎ አብነት ደምሴ ወደ ግብ ቢሞክረውም ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።

ከዚህ ሙከራ ሰባት ደቂቃዎች በኋላ የጨዋታው ውጤት ወደ አቻነት ተቀይሯል። ወላይታ ድቻዎች ያገኙትን የማዕዘን ምት በመከላከል በፈጣን መልሶ ማጥቃት ወደ ፊት ያመሩት ኢትዮ ኤሌክትሪኮች የሀብታሙ ሸዋለም ብልህነት ታክሎበት በእዮብ ገብረማርያም አማካኝነት ድንቅ ግብ አስቆጥረዋል።

ነገር ግን የኢትዮ ኤሌክትሪክ ደስታ ከአራት ደቂቃዎች መሻገር አልቻለም። ፍፁም ግርማ ከማዕዘን ያሻገረውን ኳስ ተስፋዬ መላኩ በግንባር በመግጨት ኳስ እና መረብን አገናኝቶ ቡድኑን ዳግም መሪ አድርጓል።

ከዚህ ግብ በኋላም ኢትዮ ኤሌክትሪክ የተጫዋቾች ለውጥ በማድረግም ጭምር የተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴን ለማድረግ ጥረቶችን አድርገዋል።

ቡድኑ በረጃጅም ኳሶችም የወላይታ ድቻን የተከላካይ መስመር የሚያልፉ ኳሶችን በመጣል የግብ ዕድሎች ለመፍጠር ቢጥሩም በቀላሉ ጠንካራ ሙከራዎችን ለማድረግ አልቻሉም።

በ61ኛው ደቂቃ ላይ የአቻነቱን ግብ ያስቆጠረው እዮብ ከሳጥን ውጪ የመታው ኳስ ኢላማውን ስቶ ወጥቷል።

በራሳቸው ሜዳ ላይ በቁጥር በርከት ብለው የነበሩት ወላይታ ድቻዎች በፈጣን እንቅስቃሴዎች በተለይም ከመስመር ወደ ግብ ክልል በሚሻገሩ ኳሶች ተጨማሪ ግቦችን ለማከል ሲሞክሩ ተስተውሏል።

በተለይም በ67ኛው ደቂቃ ላይ ብስራት መለሰ ከግራ መስመር ወደ መሐል የቀነሰውን ኳስ ካርሎስ ዳምጠው ከግቡ ትይዩ አግኝቶ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

ጨዋታው 84ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ የኢትዮ ኤሌክትሪኩ አምበል ሽመክት ጉግሳ ከዋና ዳኛው ጋር በነበረው የቃላት ልውውጥ በቀጥታ የቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ በጦና ንቦቹ በኩል መሳይ ሰለሞን ከቀኝ መስመር ያሻገረውን ኳስ ግዙፉ አጥቂ ካርሎስ ዳምጠው በአስደናቂ የመቀስ ምት ከመረብ አሳርፎታል።

አጥቂው በ90ኛው ደቂቃ ላይም ተጨማሪ ግብ የማስቆጠር ዕድልን ከግብ ጠባቂው ጋር ፊት ለፊት ተገናኝቶ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

የዋና ዳኛው ዳንኤል ግርማይ የጨዋታ ማጠናቀቂያ የፊሽካ ድምፅ ሲጠበቅ ተቀይሮ የገባው አሸናፊ ጥሩነህ ለኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለተኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።

ለደጋፊዎቻቸው የዘመን መለወጫ በዓል የሶስት ነጥብ ያበረከቱት ወላይታ ድቻዎች ከሁለት በላይ ግቦችን አስቆጥረው በሊጉ ድል ሲያደርጉ ከ32 ጨዋታዎች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

በሁለተኛው ሳምንት ጨዋታዎች መስከረም 16(ሀሙስ) ምሽት 1:00 ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ቡና እንዲሁም መስከረም 18(ቅዳሜ) ምሽት 1:00 ወላይታ ድቻ ከድሬዳዋ ከተማ ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በፍፁም አለሙ ብቸኛ ግብ ድል አድርገዋል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | የተባረክ ሄፋሞ ብቸኛ ግብ ሀዋሳ ከተማን የደርቢው አሸናፊ አድርጓል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዝውውር ዜናዎችየኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንዜናዎችአርባምንጭ ከተማ

አርባምንጭ ከተማ የተከላካይ አማካይ አስፈርሟል

Fitsum Nigusse By Fitsum Nigusse 2 years ago
ጅማ አባጅፋር የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች አስፈርሟል !!
“ግለሰቦች ዕውቅና ቢነፈጉኝም ውለታ አዋቂው የስፖርት ቤተሰቡና ህዝቡ ቀድሞ ስለሸለመኝና ዕውቅና ስለሰጠኝ እጅ እነሳለሁ”ኢንስትራክተር አብርሃም መብራቱ
መቻል ከተጫዋቹ ጋር ሲለያይ የመስመር አጥቂው ለመለያየት ጥያቄ አቀረበ
ታሪካዊው ክለብ በውስብስብ ፈተናዎች ውስጥ እስከ መቼ ?
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?