By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በፍፁም አለሙ ብቸኛ ግብ ድል አድርገዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ወልዋሎዜናዎችባህርዳር ከተማየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በፍፁም አለሙ ብቸኛ ግብ ድል አድርገዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የአንደኛ ሳምንት አራተኛ መርሐግብር ባህርዳር ከተማን ከወልዋሎ አዲግራት አገናኝቶ ፍፁም አለሙ ባስቆጠረው ብቸኛ ግብ የጣና ሞገዶቹ ሶስት ነጥቡን ወስደዋል።

ምሽት 1:00 ጀምሮ የተደረገው ጨዋታ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ቀዝቀዝ ባለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ ቢጀምርም በቀጣዮቹ ደቂቃዎች ላይ የግብ ዕድሎችን ለመመልከት ችለናል።

በአሰልጣኝ ደግአረግ ይግዛው በሚመራው ባህርዳር ከተማ በኩል በተለይም በመስመሮች ከወንድወሰን በለጠ እና ቸርነት ጉግሳ በሚነሱ ኳሶች የወልዋሎ አዲግራትን ተከላካይ ለመፈተን ችለዋል።

በ11ኛው ደቂቃ ላይ ባህርዳር ከተማዎች ቀዳሚውን የግብ ዕድል ሲፈጥሩ ፍፁም አለሙ የወልዋሎ አዲግራትን የኳስ ምስረታ አቋርጦ ያገኘውን ኳስ አቤል ማሙሽ ወደ ግብ ሞክሮ የነበረ ቢሆንም በግብ ጠባቂው በረከት አማረ በቀላሉ ተመልሷል።

- ማሰታውቂያ -

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ ከሳጥኑ በቅርብ ርቀት የተገኘውን ኳስ ፍፁም አለሙ ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ አድርጎ በድጋሚ በበረከት እጆች ላይ አርፏል።

በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ የሚመሩት ወልዋሎ አዲግራቶች በተለይም ወደ ፊት ገፍቶ የሚመጣውን የባህርዳር ከተማ የኋላ መስመር በፈጣን ቅብብሎሽ ሰብሮ በማለፍ እድሎችን ለመፍጠር ተደጋጋሚ ጥረቶች ቢያደርጉም ውጤታማ አልነበሩም።

ቡድኑ በአጋማሹ ቀዳሚውን የግብ ሙከራ በ16ኛው ደቂቃ ላይ ያደረገ ሲሆን ዳዋ ሆጤሳ ከፍሬው ሰለሞን የነጠቀውን ኳስ ከቡልቻ ሹራ ጋር አንድ ሁለት ተቀባብሎ ወደ ግብ ቢሞክርም ሙከራው ኢላማውን ሳይጠብቅ ቀርቷል።

ወደ ተጋጣሚ ሳጥን በመግባት የተሻሉ ሆነው የቀጠሉት ባህርዳር ከተማዎች በ18ኛው ደቂቃ ላይ ቸርነት በግራ መስመር ወደ ሳጥን ይዞ የገባውን ኳስ በአቤል ማሙሽ በኩል አልፎ ፍፁም ወደ ግብ አክርሮ ቢመታውም ከግቡ አናት በላይ ወጥቷል።

ጨዋታው 25ኛ ደቂቃ ላይ ሲደርስ የባህርዳር ከተማዎች ተደጋጋሚ ጥረት ፍሬ አፍርቶ ግብ አስቆጥረዋል። ፍሬው ሰለሞን ከዳዋ ሆጤሳ የነጠቀውን ኳስ ወንደወሰን በለጠ በቀኝ መስመር ይዞ በመግባት ለፍፁም አለሙ አቀብሎት ፍፁም ከመረብ አሳርፎታል።

ከመቻል የሁለት አመታት ቆይታ በኋላ ዳግም ወደ ባህርዳር ከተማ የተመለሰው ፍፁም አለሙ የካቲት 21/2014(936 ቀናት በኋላ) ኢትዮጵያ ቡና ላይ ካስቆጠረው ግብ በኋላ በባህርዳር ከተማ መለያ የመጀመሪያውን ግብ አስቆጥሯል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ ሶስት ያህል ደቂቃዎች ሲቀሩ ሙጂብ ቃሲም በረጅም የመታውን ኳስ በረከት አማረ ከግቡ ክልሉ ወጥቶ በተገቢው ያላራቀውን ኳስ ቸርነት ጉግሳ አግኝቶ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

በሁለተኛው አጋማሽ በሁለቱም ቡድኖች በኩል እምብዛም ሳቢ ያልሆነ እና ከሙከራዎች የራቀ የጨዋታ ክፍለ ጊዜን አሳልፈዋል።

በወልዋሎ አዲግራት በኩል ጨዋታውን በአማካይ ስፍራ ጀምሮ የነበረው ዳዋ ሆጤሳን በፊት አጥቂነት በመጠቀም ለርሱ በሚደርሱ ኳሶች ዕድል የመፍጠር ፍላጎት ቢያሳዩም የረባ የግብ ሙከራ ማድረግ ግን አልቻሉም።

በባህርዳር ከተማ በኩል በ78ኛው ደቂቃ ላይ ቸርነት ጉግሳ ከመስመር ይዞ ገብቶ የቀነሰውን ኳስ ፍሬው ሰለሞን ቢያገኘውም በውሳኔ ችግር ዕድሉን መጠቀም ሳይችል ቀርቷል።

ከሁለት ደቂቃዎች በኀላ ወንድወሰን በለጠ ከፍሬው ሰለሞን የደረሰውን ኳስ የግብ ጠባቂው በረከት አማረን መውጣት ተከትሎ ከፍ አድርጎ የሞከረው ኳስ ኢላማውን ሳይጠብቅለት ቀርቷል።

በመጨረሻም የፍፁም አለሙ ብቸኛ ግብ ጨዋታው በባህርዳር ከተማን የ1 – 0 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በሁለተኛው ሳምንት ጨዋታዎች በመጪው መስከረም 17(አርብ) 10:00 ላይ ወልዋሎ አዲግራት ከቅዱስ ጊዮርጊስ እንዲሁም ምሽት 1:00 ጀምሮ ባህርዳር ከተማ ከአዳማ ከተማ ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ በቻርለስ ሙሴጌ እና መሐመድኑር ናስር ጥምረት ዓመቱን በድል ጀምሯል
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ካርሎስ ዳምጠው አስደናቂ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ ወላይታ ድቻ አሸንፏል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
Uncategorized

በኘሪሜየር ሊጉ  ሲዳማ ቡና መሪነቱን እሚያጠብበት እድል ሲያመክን :መከላከያ ድል ቀንቶታል !!!

Mussie Girmay By Mussie Girmay 9 years ago
የኢትዮጵያ ኘሪሜየር ሊግ 1ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ | ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ድሬዳዋ ከተማ በቀጥታ /LIVESCORE/ ይከታተሉ
“በእኔ እምነት ኢት. ቡና የፕሪምየር ሊጉ ሻምፒዮን የመሆን አቅም አለው” ወንድሜነህ ደረጄ /ኢትዮጵያ ቡና/
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በአሜሪካ የዋሊያዎቹ ጉዞ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጠ
ፍፁም ገብረማርያም ለመከላከያ ፊርማውን አኑራል።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?