By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ በቻርለስ ሙሴጌ እና መሐመድኑር ናስር ጥምረት ዓመቱን በድል ጀምሯል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችድሬዳዋ ከተማአርባምንጭ ከተማየጨዋታ ዘገባ

የጨዋታ ዘገባ | ድሬዳዋ ከተማ በቻርለስ ሙሴጌ እና መሐመድኑር ናስር ጥምረት ዓመቱን በድል ጀምሯል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

በሊጉ ሁለተኛ መርሐግብር በበርካታ ደጋፊዎቹ ፊት የተጨመወተው ድሬዳዋ ከተማ ሽኩቻዎች በበዙበት ጨዋታ አርባምንጭ ከተማን አሸንፏል።

በጨዋታው በአሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ የሚመራው ድሬዳዋ ከተማ ይበልጥ ኳስ ይዞ በመንቀሳቀስ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ሲጥር ተስተውሏል።

ቡድኑ በቁጥር በርከት ብሎም የአርባምንጭ ከተማን የተከላካይ መስመር በመፈተን ኳስ እና መረብን ለማገናኘት የነበሩት ጥረቶች በጠንካራ ሙከራ ለመታጀብ በርካታ ደቂቃዎችን አስጠብቋል።

አብዛኛውን የጨዋታ ጊዜ ከኳስ ውጪ ያሳለፉት አርባምንጭ ከተማዎች በሁለት አጋጣሚዎች ወደ ተጋጣሚ ሳጥን ሲደርሱ በተለይም 10ኛው ደቂቃ ላይ ያመከኑት ዕድል አስቆጪ ነበር።

- ማሰታውቂያ -

የግራ መስመር ተከላካዩ ካሌብ በየነ ያሻገረውን ኳስ አህብዋ ብሪያን ከግቡ ትይዩ አግኝቶ በግንባር ገጭቶ ወደ ግብ ቢልከውም ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።

ድሬዳዋ ከተማዎች ከአርባምንጭ ከተማ የተከላካይ መስመር ጀርባ በሚጣሉ እና በተለይም በቀኝ መሰመር በኩል በሚነሱ ኳሶች ዕድሎችን ለመፍጠር ደጋግመው ጥረዋል።

ብርተካናማዎቹ በ30ኛው ደቂቃ ላይ በድንቅ የአንድ ሁለት ቅብብል የአርባምንጭ ከተማን የተከላካይ መስመር በመስበር ኳስን ከመረብ አዋህደዋል።

በጥሩ ፈጣን ቅብብል በቀኝ የሳጥኑ የቀኝ ሳጥን አቅጣጫ ገብቶ መሐመድኑር ናስር ቢደርስውም ኳሱ አምልጦት ሊወጣ ሲል በግሉ ጥረት ኳሱን ለቻርለስ ሙሴጌ አቀብሎ አጥቂው ቡድኑን መሪ አድርጓል።

የመጀመሪያው የጨዋታው አጋማሽም በድሬዳዋ ከተማ የ1 – 0 መሪነት ተጠናቋል።

በርካታ ሽኩቻዎች ተደጋጋሚ የግብ ሙከራዎች እና ሁለት ግቦች ያስተናገደው አጋማሹ ልክ እንደቀዳሚው ጨዋታ ሁሉ የቀይ ካርድም አስመልክቶናል።

በአጋማሹ ዳግም ሊጉን የተቀላቀሉት አርባምንጭ ከተማዎች ከፊት ቡድኑን ለሚመራው አህመድ ሁሴን ተደጋጋሚ ኳሶችን በማድረስ በአጥቂው አማካይነት ወደ አቻ ለመምጣት ጥረዋል።

ጠንካራው አጥቂ አህመድ ሁሴንም በሚደርሱት ኳሶች በተደጋጋሚ የድሬዳዋ ከተማን ተከላካዮች እጅጉኑ ፈትኗል።

በ47ኛው ደቂቃ ላይ አህመድ ሁሴን በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ የደረሰውን ኳስ ግብ ጠባቂውን አልፎ ጭምር ለማስቆጠር ቢሞክርም አህመድ ረሺድ ደርሶ ግብ ከመሆን አድኖታል።

ጫና ማሳደራቸውን የቀጠሉት አዞዎቹ በ54ኛው ደቂቃ ላይ ጥሩ አጋጣሚ ፈጥረው ነበር። በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ እንዳልካቸው መስፍን ለአሸናፊ ተገኝ ያቀበለውን ያለቀለት ኳስ አሸናፊ ሳይደርስበት ቀርቷል።

በድሬዳዋ ከተማ በኩልም በተለይም ከመጀመሪያው አጋማሽ በአንፃራዊነት ከነበረው የቀኝ መስመር እንቅስቃሴ ወደ ግራ በማጋደል
ተደጋጋሚ ኳሶችን ወደ ሳጥን ለማድረስ ጥረቶች አድርገዋል። ሆኖም ግን በአርባምንጭ ከተማ በኩል በአህመድ ሁሴን እንደሚፈጠሩት አይነት ጠንካራ የግብ ሙከራዎች ለማድረግ ረጅም ደቂቃዎች ለመጠበቅ የግድ ብሏቸዋል።

በአዞዎቹ በኩል በ66ኛው ደቂቃ ላይ አህመድ በድጋሚ በቀኝ አቅጣጫ ያገኘውን ኳስ አክርሮ ወደ ግብ ቢመታውም ግብ ጠባቂው አብዩ ካሳዬ ተቆጣጥሮታል።

ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ድሬዳዋ ከተማዎች በቀኝ የሳጥኑ አቅጣጫ በጀሚል ያዕቆብ አማካይነት ያደረጉት የግብ ሙከራ ኢላማውን መጠበቅ አልቻለም።

የአህመድ ሁሴን ጥረት በ80ኛው ደቂቃ ላይ ፍሬ ሲያፈራ አጥቂው ከእንዳልካቸው መስፍን የደረሰውን ኳስ በጥሩ አጨራረስ ከመረብ አሳርፏል።

በጨዋታው አልፎ አልፎ የነበሩት ሽኩቻዎች ይበልጥ እየጎሉ በመጡበት የጨዋታው የመጨረሻ ደቂቃዎች በርካታ ክስተቶችን አስመልክተውናል።

የአቻነቱ ግብ ከተቆጠረ አምስት ደቂቃዎች በኋላ ብርቱካናማዎቹ ዳግም መሪ ሆነዋል። በዚህ ግብ ለድሬዳዋ ከተማ ቀዳሚ ግብ መቆጠር አቀባይ እና አስቆጣሪ የሆኑት ተጫዋቾች ሚና ተለዋውጠው ቡድናቸውን መሪ አድርገዋል።

በግራ መስመር የነበረው የመጀመሪያው ግብ አስቆጣሪ ቻርለስ ሙሴጌ ከአቡበከር ሻሚል የደረሰውን ኳስ ወደ መሐል ሲቀንሰው መሐመድኑር ናስር አስቆጥሮታል።

ግቡ በተቆጠረበት ወቅት በጨዋታው ዋና ዳኛ ያልተገባ ባህሪ ያሳየው አበበ ጥላሁን በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

በ87ኛው ደቂቃ ላይ አርባምንጭ ከተማዎች በፈጣን እንቅስቃሴ ወደ ተጋጣሚ ሜዳ ይዘው የገቡትን ኳስ ግብ ጠባቂው ከግቡ ርቆ ወጥቶ አብዩ ካሳዬ በመለሰበት ወቅት በእጁ ነክቷል በሚል ከፍተኛ ተቃውሞዋቸውን ገልፀዋል።

በዚህ አጋጣሚ ድሬዳዋ ከተማዎች በፈጣን ይዘው የገቡትን ኳስ መሐመድኑር ናስር ግብ ጠባቂው ኢድሪስ ኦጎዶጆን አልፎ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ኳስና መረብን ማዋሀድ ሳይችል ቀርቷል።

በ90ኛው ደቂቃ ላይ ሙሉጌታ ካሳሁን እንዲሁም በ90+6 ላይ አህመድ ሁሴን ወደ ግብ ያደረጓቸው ኢላማቸውን የጠበቁ የግብ ሙከራዎች የአብዩ ካሳዬን እጆች ማለፍ አልቻሉም።

በመጨረሻም ድሬዳዋ ከተማ በአሰልጣኝ ይታገሱ እንዳለ እየተመራ የመክፈቻ ጨዋታውን በ2 – 1 ድል ፈፅሟል።

በሁለተኛ ሳምንት ጨዋታዎች መስከረም 15 ቀን 10:00 አርባምንጭ ከተማ ከኢትዮጵያ መድኅን እንዲሁም መስከረም 18 ምሽት 1:00 ጀምሮ ድሬዳዋ ከተማ ከወላይታ ድቻ ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article “የሰራናቸው ስህተቶች እስከመጨረሻው በጫና እንድንጨርስ አድርጎናል።” አሰልጣኝ ግርማ ታደሰ “የተከላካይ ክፍላችን በመጀመሪያው አጋማሽ የፈረሰ ነበር።” አሰልጣኝ ዳንኤል ፀሐዬ
Next Article የጨዋታ ዘገባ | የጣና ሞገዶቹ በፍፁም አለሙ ብቸኛ ግብ ድል አድርገዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
አፍሪካ ሻምፒየንስ ሊግአፍሪካዜናዎች

ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል አርቢተር ባምላክ ተሰማ ወዮሳ የአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ እንዲመራ ተመረጠ

Mussie Girmay By Mussie Girmay 8 years ago
ናትናኤል ዘለቀ ከፈረሰኞቹ ጋር እስከ 2011 እሚያቆየውን ፊርማ አኑሯል!!
“የምንከተለው የአጨዋወት ፍልስፍናና የአቡኪ ልዩነት ፈጣሪ ተጨዋች መሆን በርካታ ግቦችን እንድናስቆጥር አድርጎናል”ዊሊያም ሰለሞን /ኢትዮጵያ ቡና/
በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ምክንያት ይቋረጣል ተብሎ የነበረው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መቼ እንደሚካሔድ ታውቋል።
ኤሊያስ ማሞ ወደ አዳማ ከተማ አቅንቷል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?