By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: መቻል ከሦስት ሽንፈት ወደ ድል ሲመለስ ፈረሰኞቹ በጎል ደምቀው አሸንፈዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ
ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ወልዋሎ ዜናዎች
ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ
ዜናዎች ሀዋሳ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ድሬዳዋ ከተማ አዳማ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ ሀዲያ ሆሳዕና የጨዋታ ዘገባ
ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ
ዜናዎች ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስሀዋሳ ከተማድሬዳዋ ከተማአርባምንጭ ከተማሲዳማ ቡናአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባመቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡና

መቻል ከሦስት ሽንፈት ወደ ድል ሲመለስ ፈረሰኞቹ በጎል ደምቀው አሸንፈዋል

ቴዎድሮስ ታከለ
ቴዎድሮስ ታከለ 2 months ago
Share
SHARE

በአዲስ አበባ እና አዳማ በተደረጉ አራት ጨዋታዎች መቻል ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ሲመለስ ቅዱስ ጊዮርጊስ በጎል ፌሽታ ደምቆ ተጋጣሚውን ረቷል። መሪው ሲዳማ ነጥብ ሲጥል ቡናማዎቹ እና ሐይቆቹ ነጥብ ተጋርተዋል።

አርባምንጭ ከተማ 0-2 መቻል

የመቻሎች የበላይነት ገዝፎ ከጅምሮ ገዝፎ በታየበት ጨዋታ አርባምንጮች ከይገዙ ቦጋለ የርቀት ሙከራ በስተቀር በተጋጣሚያቸው ጥቃቶችን ደጋግመው አስተናግደው። በጥልቅ እንቅስቃሴዎች በቸርነት ጉግሳ ሁለት ፣ በአለምብርሀን ይግዛው እና አብዱልከሪም ወርቁ አማካኝነት ያለቀላቸውን ሙከራዎች መቻሎች ፈጥረው የነበረ ቢሆንም በቶጓዊው የግብ ዘብ እድሪሱ ኦጎዶጆ ብርቱ ጥረቶች አዞዎቹ ጎል እንዳይቆጠርባቸው ሆኗል።

ከዕረፍት መልስ ፈጣን በሆኑ ሽግግሮች ወደ ውስጥ ተስቦ በመጫወት አንዳች ነገርን ለመፍጠር ጥረት ማድረጋቸውን የቀጠሉት ጦረኞቹ እንደነበራቸው የእንቅስቃሴ ብልጫ 68ኛው ደቂቃ ላይ ጎል አግኝተዋል። 68ኛው ደቂቃ ላይ በጨዋታው ደምቆ መታየት የቻለው አለምብርሀን ይግዛው ወደ ሳጥን ኳስን ይዞ ሲገባ በተከላካዩ አካሉ አትሞ ጥፋት ስለተሰራበት የዕለቱ ዋና ዳኛ ኤፍሬም ደበሌ የሰጡትን የፍፁም ቅጣት ምት ቸርነት ጉግሳ ከመረብ አዋህዶ ቡድኑን ቀዳሚ አድርጓል። ጨዋታው ቀጥሎ ሊጠናቀቅ በተሰጠው ጭማሪ አምስት ደቂቃዎች ውስጥ 90+1 ደቂቃ ላይ አለምብርሀን ይግዛው በጥሩ ዕይታ ያመቻቸለትን ኳስ ተቀይሮ የገባው ዩጋንዳዊው አጥቂ ቻርለስ ሙሴጌ እድሪሱ መረብ ላይ አስቀምጧታል። ጨዋታው ሊገባደድ ሲቃረብ በሌላ አጋጣሚ የአብስራ ተስፋዬ ከአለምብርሀን የተቀበለውን ኳስ መጠቀም ሳይችል በመጨረሻም ጨዋታው መቻልን ከሦስት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ ድል መልሷል።

- ማሰታውቂያ -

ቅዱስ ጊዮርጊስ 4-0 ድሬዳዋ ከተማ

ተመጣጣኝ የሚመስል አጀማመርን ማየት ብንችልም በሂደት ግን የቅዱስ ጊዮርጊሶች የበላይነትን መታየት በቻለበት ጨዋታ 16ኛው ደቂቃ ላይ ነበር ጎል መቆጠር የቻለው። የድሬዳዋው ተከላካይ የአብስራ ሙሉጌታ የተሳሳተውን ኳስ ያገኘው ተገኑ ተሾመ ጥሩ በሆነ መልኩ ሲያቀብለው ወጣቱ አማካይ ሀብታሙ ጉልላት ከቀኝ ሳጥን ውስጥ ሆኖ ጎሉን መረቡ ላይ አዋህዷል። በጎሉ መመራታቸው ድንጋጤ ውስጥ የከተታቸው ብርቱካናማዎቹ ይባስ ብለው 22ኛው ደቂቃ ላይ አማካዩ ሔኖክ ሀሰን የአብስራ ጎሳዬ ላይ በሰራው ጥፋት የዕለቱ ዋና ዳኛ ሙሉቀን ያረጋል በቀጥታ ቀይ ሊያሰናብቱት ችለዋል። 35ኛው ደቂቃ ላይ ቶሎሳ ንጉሴ ከቀኝ ወደ ውሰጥ ሲያሻማ አብዱሰላም የሱፍ ኳስን በእጅ በመንካቱ በዕለቱ ሁለተኛ ረዳት ዳኛ ትግል ግዛው ዕገዛ የተገኘን የፍፁም ቅጣት ምት አቤል ያለው አስቆጥሯታል።

ከዕረፍት መልስ ከቆሙበት የቀጠሉት ቅዱስ ጊዮርጊሶች 49ኛው ደቂቃ ላይ ከቀኝ አቤል ያገኘውን ኳስ ከፍ በማድረግ ሲሰጠው ፍፁም ጥላሁን በግንባር ገጭቶ የአብዩ ካሳዬ መረብ ላይ ሦስተኛዋን ጎል አገናኝቷል። በጎልም ሆነ በተጫዋች የቁጥር ብልጫ ተወስዶባቸው ጨዋታውን የቀጠሉት ድሬዳዋ ከተማዎች 88ኛው ደቂቃ ላይ አቤል ያለው የተሰነጠቀለትን ኳስ አህመድ ረሺድን በፍጥነት ቀድሞ አስደናቂ ጎል በማስቆጠር ጨዋታው በመጨረሻም በፈረሰኞቹ 4ለ0 በሆነ አሸናፊነት ተቋጭቷል።

ኢትዮጵያ ቡና 1-1 ሀዋሳ ከተማ

ጥሩ ፉክክርን ከጅምሩ ያስመለከተን ጨዋታ ሻባን መሐመድ ለኢትዮጵያ ቡና ሽመልስ በቀለ እና አብነት ደምሴ ለሀዋሳ ጠጣር የሆኑ ሙከራዎችን ቢያደርጉም በተሻለ የማጥቃት ደመ ነብስ የተሞሉት ቡናማዎቹ 38ኛው ደቂቃ ናይጄሪያዊው አማካይ ዲቫይን ዋቹኩዋ ከወጣቱ ናትናኤል ፍሬው ያገኛትን ኳስ ወደ ጎልነት በድንቅ አጨራረስ አስቆጥሮ ቡድኑን ቀዳሚ አድርጓል።

ከዕረፍት መልስ ኢትዮጵያ ቡናዎች የበላይ ሆነው በቀረቡበት አጋማሽ ተደጋጋሚ ጥቃቶችን ሰንዝረው ሌላ የግብ ዕድል ያመለጣቸው ሲሆን ጨዋታው ተጠናቆ በተሰጠው የጭማሪ ደቂቃ ላይ 90+3 ላይ ከእጅ ውርወራ መነሻዋን አድርጋ ጌታነህ ከበደ ከተባረከ ሄፋሞ የተቀበለውን ኳስ የቡናማዎቹ የመከላከል ስህተት ታክሎ ሀዋሳን አቻ በማድረግ 1ለ1 ጨዋታው ተቋጭቷል።

አዳማ ከተማ 2-2 ሲዳማ ቡና

አጀማመራቸው ተቀራራቢ ቢመስልም ወደ ግራ በማዘንበል መስፍን ታፈሠን ለመጠቀም አልመው የተጫወቱት ሲዳማ ቡናዎች 16ኛው ደቂቃ ከማዕዘን ምት ፍቅረየሱስ ተወልደብርሀን አሻምቶ ብርሀኑ በቀለ በግንባር ጨርፎለት መስፍን ታፈሠ ተንሸራቶ ቀዳሚዋን ጎል አስቆጥሯል። በእንቅስቃሴ ብልጫ ባይወሰድባቸውም በተቃራኒው ጎል አካባቢ ሲደርሱ ደካማ ሆነው የታዩት አዳማዎች 44ኛው ደቂቃ ፍቅረየሱስ ከደግፌ ያገኘውን ኳስ በጥሩ ዕይታ ሰጥቶት ሳጥን ውስጥ ኳሷን ያገኘው መስፍን ታፈሠ ለራሱም ሆነ ለቡድኑ ሁለተኛ ጎል አድርጓታል። ቢኒያም አይተን ከአንድ ደቂቃ በኋላ ጥሩ አጋጣሚን ለአዳማ ፈጥሮ የግብ ዘቡን በቀላሉ አሳቅፎታል።

ከዕረፍት መልስ 55ኛው ደቂቃ ላይ የሲዳማ ቡና ተጫዋቾች በሰሩት ስህተት አቡበከር ሳኒ አዳማን ወደ ጨዋታ የመለሰች ጎል አስቆጥሯል። ጨዋታው ከፍ ባለ ተነሳሽነት ቀጥሎ ሊጠናቀቅ በተሰጠው ጭማሪ 90+1 ደቂቃ ላይ ከማዕዘን ምት የተሻማን ኳስ ሙጂብ ቃሲም በእግር ኳስ ህይወቱ መነሻ የነበረው አሳዳጊ ክለቡ መረብ ላይ አሳርፎ አዳማን አቻ አድርጓል። ተጫዋቹም ጎሏን አስቆጥሮ ደስታውን ሲገልፅ በቀደመ ክለቡ ደጋፊዎች ተቃውሞን አስተናግዷል። ጨዋታው ሊጠናቀቅ በሁለት ደቂቃ ልዩነት ውስጥ ቢኒያም አይተን ለአዳማ ብርሀኑ በቀለ ለሲዳማ ካደረጓቸው እና ብረት በተመሳሳይ ከመለሳቸው ሙከራዎች በኋላ ጨዋታው ተጠናቋል።

You Might Also Like

ሀዋሳ ከተማ ወጣቱን የቀድሞው የግብ ዘቡን አስፈረመ

ወልዋሎዎች አማካዩን የግላቸው አደረጉ

ሀዋሳ ከተማ ሁለገቡን ተጫዋች አስፈረመ

ድሬዳዋ ከተማ ወሳኝ ድል ሲቀናጅ ሀድያ ሆሳዕና እና አዳማ ነጥብ ተጋሩ

ሲዳማ ቡና ከአበባየው ሀጂሶ ጋር ተለያየ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
Previous Article ሀድያ ሆሳዕና እና ኤሌክትሪክ ሦስት ነጥብን ከተጋጣሚያቸው ላይ ሸምተዋል
Next Article የ15ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

አርባምንጭ ሶስተኛውን አዲስ የክለቡን ፈራሚ አግኝቷል ።

Fitsum Nigusse By Fitsum Nigusse 2 years ago
“ከ2019ኙ የዓለም የሴቶች ዋንጫ በኋላ ዳኝነት [በቃኝ]” “ዳኝነት በውጪ ያጓጓል፤ በሀገር ውስጥ ግን ያደክማል” ኢንተርናሽናል አልቢተር ሊዲያ ታፈሰ
የምስራቅ እና መካከለኛው የአፍሪካ ሀገራት ከ23 ዓመት በታች ውድድር አዘጋጅ ብሔራዊ ኮሚቴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ፡፡
አሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸው ከጅማ አባጅፋር ጋር የነበረውን ውል ቀዷል
መቐለ 70 እንደርታ ሶስት ጨዋታ በፎርፌ ተሸናፊ እንዲሆን ሲወሰን በተጨማሪም ሀያ ሺ ብር ቅጣት ተጥሎበታል!!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?