አዲስ አበባ እና አዳማ የነበሩ ሁለት ጨዋታዎች በተመሳሳይ 0ለ0 ተቋጭተዋል።
ባህርዳር ከተማ 0-0 መቐለ 70 እንደርታ
በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ስታዲየም ሁለቱን ቡድኖች ያገናኘው መርሀግብር በመጀመሪያዎቹ ሰላሳ ደቂቃዎች መቐለዎች ረጃጅም ኳሶችን በመጠቀም በይበልጥ የተሻለውን ጊዜ ማሳለፍ ችለዋል። 10ኛው ደቂቃ ላይ በረጅሙ በተጋጣሚ ሜዳ የተጣለን ኳስ በተከላካይ በግንባር ተገጭቶ ሲመለስ ኪቲካ ጀማ አግኝቶ ሲመታው የግብ ዘቡ ፔፕ ሰይዶ አምክኖበታል። ከአስራ ሦስት ደቂቃዎች መልስም አሁንም በረጅሙ ወደ ሳጥን የተጣለን ኳስ ብርሀኑ አዳሙ አመቻችቶለት አሸናፊ ሀፍቱ በግልፅ ያገኛትን መልካም ዕድል በቀላሉ አምክኗታል።
ዘግየት ብለው ቢሆን ወደ ጨዋታው ገብተው በሽግግር ጥቃት መሰንዘር የጀመሩት ባህርዳሮች 35ኛው ደቂቃ ከግራ የሜዳው ክፍል ኩዋሜ ቦአቲንግ የመታውን የግብ ዘቡ መሐመድ ዛጉዌ ለመያዝ ጥረት ሲያደርግ የወጣችበት ጨዋታው ሊጋመስ ሲቃረብ 45ኛው ደቂቃ ላይ ሔኖክ ይበልጣል በጥሩ ቅብብል ከቦአቲንግ የደረሰችውን ኳስ ከሳጥኑ ጠርዝ አክርሮ መቶ የግቡ የቀኝ ቋሚ ብረትን ኳሷ ለትማ ስትመለስ ኩዋሜና ቦአቲንግ ያገኛትን የምታስቆጭ አጋጣሚ ወደ ውጪ ሰዷታል።
- ማሰታውቂያ -
ባህርዳሮች የተሻለ አጋማሽን ባሳለፉበት ሁለተኛው አጋማሽ ቡድኑ በሔኖክ ይበልጣል እና ወንድወሰን በለጠ እንዲሁም ኩዋሜና ቦአቲንግ አማካኝነት ብርቱ ጥረት ማድረግ ቢችሉም የጠራችውን ሙከራ ያስመለከቱን ግን መቐለዎች ናቸው። 82ኛው ደቂቃ ላይ ከማዕዘን ምት ፍፁም አለሙ ሲያሻማ ደስታ ዮሐንስ ነፃ ሆኖ ያገኘውን ኳስ ወደ ጎል ሞክሯት ፔፕ ከመለሳት በኋላ ጨዋታው ጎል ሳይቆጠርበት 0ለ0 ተቋጭቷል።
ኢትዮጵያ መድን 0-0 ወልዋሎ ዓ/ዩኒቨርስቲ
ኢትዮጵያ መድኖች የበላይነቱን በያዙበት የመጀመሪያው አጋማሽ በይበልጥ የተጋጣሚያቸው የመጨረሻ ሜዳ አብዛኞቹን ደቂቃዎች ቢያሳልፉም በጎል መታጀብ ግን ሳይችሉ ቀርተዋል። 13ኛው ደቂቃ ረመዳን የሱፍ ከሳጥን ውጪ አክርሮ መቶ ግብ ጠባቂው ሙታክብዋ ጆኤል ባመከናት አደገኛ ሙከራ ጥቃት መሰንዘር የጀመሩ ሲሆን 19ኛው ደቂቃ ላይም አለን ካይዋ በግብ ዘቡ ሌላ ሙከራ ተመክቶበታል። ወደ ኋላ አፈግፍገው በተጋጣሚያቸው የሚሰነዘርባቸውን ጥቃት መከላከል ላይ ተጠምደው የቆዩት ወልዋሎዎች 34ኛው ደቂቃ ጎል ለማስተናገድ ተቃርበው ነበር በጥሩ ቅብብል ከበረከት ካሌብ ጋር ረመዳን የሱፍ አድርጎ ያቀበለውን ወገኔ ገዛኸኝ ወደ ግብ መቶ ዩጋንዳዊው ግብ ጠባቂ ሙታክብዋ ጆኤል መረብ ላይ ልታርፍ የነበረችውን ዕድል በጥሩ ብቃት አድኖበታል።
ከዕረፍት መልስ ተሻሽለው የተመለሱት ወልዋሎዎች በረጃጅም ኳስ ተደራሽ በሚያደርጓቸው ኳሶች አንዳች ነገርን ለመፍጠር ጥረት ቢያደርጉም ለፋሲል
ገብረሚካኤል ብዙም ከባዶች አይደሉም። 63ኛው ደቂቃ በየነ ባንጃው ከማዕዘን አሻምቶ ኮንኮኒ ሀፊዝ በግንባር ገጭቶ ግብ ጠባቂው ፋሲል ገብረሚካኤል ካወጣት አንድ በጥራት ከተሞላች ሙከራ በቀር ሳንመለከት ጨዋታው ያለ ጎል ተጠናቋል።


