የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ሄኖክ አርፊጮ (ሀዲያ ሆሳዕና) : ክለቡ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ14ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 72 ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀሙ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት ቀርቦበታል ።
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. ቢንያም ሀብታሙ (ኢትዮጵያ ቡና) /ግጠ አሰልጣኝ/ : ክለባቸው ከ ፋሲል ከነማ ጋር ባደረገው የ14ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ በ 8ዐ ኛ ደቂቃ ላይሁለተኛ ቢጫ ካርድ የሚያስጥ ጥፋት በመፈፀማቸው በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገዱ ስለሆኑ ሪፖርት ቀርቦባቸዋል ። ስለሆነም የቡድን አመራሩ ለፈፀሙት ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የውድድር ደንብ የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀፅ 13 ንዑስ አንቀጽ 13.3 ተቁ 15
መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገዱ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 እንዲከፍሉ የየውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. መሐመድኑር ናስር (ድሬደዋ ከተማ): በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል።
- ማሰታውቂያ -
- ድሬደዋ ከተማ-ምድረ ገነት ሽረ
- መቻል-ድሬደዋ ከተማ
- ኢትዮጵያ ቡና-ድሬደዋ ከተማ
- ድሬደዋ ከተማ-ኢትዮ ኤሌትሪክ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
4. ቃለአብ ውብሸት (ሀዲያ ሆሳዕና) የመታወቂያ ቁጥር EFF-18-612 በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም ከታች በተጠቀሱት 4 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል።
- ባህርዳር ከተማ-ሀዲያ ሆሳዕና
- ኢትዮጵያ ቡና-ሀዲያ ሆሳዕና
- መቐለ 70 እንደርታ-ሀዲያ ሆሳዕና
- ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሀዲያ ሆሳዕና
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
5. ሀዲያ ሆሳዕና ክለቡ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ባደረገው የ14 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የሀዲያ ሆሳዕና ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- ቃለአብ ውብሸት
- ሙሴ ከበላ
- ሄኖክ አርፊጮ
- ሄኖክ አርፊጮ
- ሱራፌል ጌታቸው
- ኢዮብ አለማየሁ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
6. ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ክለቡ ከአዳማ ከተማ ጋር ባደረገው የ14 ኛ ሳምንት እግርኳስ ጨዋታ የወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲ ቡድን ተጫዋች የሆኑት
- ብሩክ እንዳለ
- ኪም ላም
- ስምዖን ማሩ
- ሙታክብዋ ጆኤል
- ኪሩቤል ወንድሙ
በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 3 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 65 (ሀ) መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
7. አርባምንጭ ከተማ ክለቡ ከሲዳማ ቡና ጋር ባደረገው የ14ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ ከዕረፍት መልስ ጨዋታው 5 ደቂቃ ዘግይቶ ለመጀመሩ ምክኒያት ስለመሆኑ ሪፖርት ተደርጓል።
ስለሆነም ክለቡ ላጠፋው ጥፋት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የውድድርና ስነስርዓት የውድድር ደንብ ክፍል 1 አንቀጽ 13 ንዑስ አንቀጽ 13.2 በተራ ቁ. 17 እና 18
መሰረት ብር 15000 / አስራ አምስት ሺህ/ እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል፡፡
8. ኢትዮጵያ ቡና ክለቡ ከፋሲል ከነማ ጋር በነበረው የ14ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ መርሃ ግብር የክለቡ ደጋፊዎች 22/ሀያ ሁለት/ የስታድየም ወንበሮች ላይ በመስበርና በማወላለቅ ጉዳት ስለማድረሳቸው ሪፖርት ተደርጓል። ስለሆነም ክለቡ ጉዳት የደረሰባቸውን ወንበሮች እንዲያሰራ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍል ወስኗል፡፡


