መቐለ 70 እንደርታ ድል ሲቀናው የጣና ሞገዶቹ እና ብርቱካናማዎቹ ጨዋታ 0ለ0 ተጠናቋል።
መቐለ 70 እንደርታ በተሻለ የማጥቃት ደመ ነብስን ይዘው በገቡበት የመጀመሪያዎቹ ሰላም ደቂቃዎች ሁነኛ የጥቃት ምንጫቸውን ፍፁም አለሙን በማድረግ በይበልጥ በጥልቀት በመንቀሳቀስ 25ኛው ደቂቃ ላይ ጎል አስቆጥረዋል። መድኖች በቅብብል ወቅት የተሳሳቱትን ኳስ ሙሉጌታ ከፍፁም ጋር በጥሩ የእግር ስራ ሙሉጌታ ወልደጊዮርጊስ በመጨረሻም ከግራ ሳጥን ውስጥ የላካትን ኳስ ያሬድ ካሳዬ ለማውጣት ጥረት ሲያደርግ ፍፁም አለሙ እግር ስር የገባችውን ኳስ አማካዩ መረቡ ላይ አሳርፎ ቡድኑን መሪ አድርጓል።
ከዕረፍት በፊት በብዙ ረገድ ለመበለጥ የተገደዱት መድኖች በተሻሻለ አቀራረብ በተመለሱበት ሁለተኛው አጋማሽ በእንቅስቃሴ ጥሩ ቆይታን ቢያደርጉም ብሩክ ሙሉጌታ እና አለን ካይዋ ካደረጓቸው ሁለት ጠጣር ሙከራዎች በቀር ጎልን ሳያስመለክን በመጀመሪያ አጋማሽ ብቸኛ ጎል መቐለን 1ለ0 አሸናፊ አድርጎ ተጠናቋል።
አዲስ አበባ ስታዲየም ላይ የተደረገው እና በውድድር ዘመኑ የወጥነት ችግር የሚታይባቸው ባህርዳር ከተማ እና ድሬዳዋ ከተማ ያደረጉት ጨዋታ ጎል እና መረብ መገናኘት ሳይችሉ 0ለ0 ተጠናቋል።
- ማሰታውቂያ -



