የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
1. ዘነበ ከድር (ሸገር ከተማ) : ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድ ተመልክቷል።
- ሸገር ከተማ-አዳማ ከተማ
- ነገሌ አርሲ-ሸገር ከተማ
- ወላይታ ድቻ-ሸገር ከተማ
- ሸገር ከተማ-ሃዋሳ ከተማ
- ሸገር ከተማ-ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
2. መስፍን ታፈሰ (ሲዳማ ቡና): ከታች በተጠቀሱት 5 ጨዋታዎች የቢጫ ማስጠንቅቂያ ካርድተመልክቷል።
- ማሰታውቂያ -
- ሲዳማ ቡና-ወላይታ ድቻ
- ምድረ ገነት ሽረ -ሲዳማ ቡና
- ሲዳማ ቡና-መቐለ 70 እንደርታ
- መቻል-ሲዳማ ቡና
- ሀዲያ ሆሳዕና-ሲዳማ ቡና
ስለሆነም ተጫዋቹ ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ ክፍል 2 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 35(ሠ) መሰረት 1 ጨዋታ እንዲታገድ በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 1500 እንዲከፍል የውድድርና ስነስርዓት ኮሚቴ ወስኗል።
3. ኢትዮጵያ ቡና ክለቡ ከምድረ ገነት ሽረ ጋር በነበረው የ13ኛ ሳምንት እግር ኳስ ጨዋታ መርሃ ግብር የክለቡ ደጋፊዎች 15/አስራ አምስት/ የስታድየሙን ወንበሮች ስለመስበራቸው ሪፖርት ተደርጓል። ስለሆነም ክለቡ የተሰበሩትን ወንበሮች እንዲያሰራ ወይም የስታድየሙ ባለቤት አሰርቶ የሚያቀርበውን ዋጋ እንዲከፍል ወስኗል፡፡


