By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: መሪው ሲዳማ ቡና ነጥብ ሲጥል መቻል ወደ ድል ተመልሷል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
መቻልየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችሲዳማ ቡናአዳማ ከተማየጨዋታ ዘገባኢትዮጵያ መድህን

መሪው ሲዳማ ቡና ነጥብ ሲጥል መቻል ወደ ድል ተመልሷል

ቴዎድሮስ ታከለ
ቴዎድሮስ ታከለ 2 months ago
Share
SHARE

ሲዳማ ቡና መሪነቱን የሚያጠናክርበትን ዕድል ሲያመክን መቻል ድል ቀንቶታል።

አዳማ ከተማ 1-3 መቻል

የአዲስ አበባ ስታዲየም ያስተናገደው የመጨረሻ ቀን ብቸኛ ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ በይበልጥ ከአማካይ ክፍል በመነሳት ወደ መስመር ለጥጠው መጫወትን መርጠው ከተጋጣሚያቸው አዳማ በተሻለ መንቀሳቀስ የቻሉት መቻሎች 21ኛው ደቂቃ ላይ ሀይደር ሸረፋ ከእግሩ ያመለጠችውን ኳስ ቻላቸው መንበሩ አግኝቶ ወደ ሳጥን ሲልካት በቸርነት ጉግሳ ተጨርፋ መሐመድ አበራ ጋር ስትደርስ አጥቂው ወደ ጎልነት ለውጦ መቻልን ቀዳሚ አድርጓል።

አዳማ ከተማዎች በሽግግር በመንቀሳቀስ የመጨረሻው ሜዳ ላይ መድረስ ቢችሉም በሚያሳዩት የውሳኔ ልልነት በተቃራኒው በድጋሚ ጎል ተቆጥሮባቸዋል። 45+2 ደቂቃ ላይ አብዱልከሪም ወርቁ በአግባቡ መሐል ለመሐል የሰጠውን ኳስ መሐመድ አበራ ለበረከት ደስታ በድንቅ እይታ ሰጥቶት ተጫዋቹ መድሀኔ ብርሀኔ እና ሙጂብ ቃሲም እንዲሁም የግብ ዘቡን አላዛር ማርቆስን ጭምር በማለፍ ከመረብ አሳርፏል።

- ማሰታውቂያ -

ከዕረፍት መልስ ጨዋታው ሲቀጥል ከቆሙበት የቀጠሉት መቻሎች የጎል መጠናቸውን ከፍ ያደረገች ጎልን 63ኛው ደቂቃ ላይ አክለዋል። በረከት ደስታ ከማዕዘን ያሻማውን ኳስ ከቁመታሞቹ የአዳማ ተከላካዮች መሐል ዘሎ መሐመድ አበራ ለራሱ ሁለተኛ ለቡድኑ ሦስተኛዋን ጎል በግንባር አስቆጥሯል። ሦስት ጎሎችን ካስተናገዱ በኋላ ዘግይተው ወደ ጨዋታ ለመመለስ ጥረት ማድረግን በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች የሞከሩት አዳማ ከተማዎች የመቻሉ የግብ ዘብ ከራሱ ሜዳ ለቆ መውጣቱን ተከትሎ አህመድ ሁሴን ከረጅም ርቀት 85ኛው ደቂቃ ላይ ከሽንፈት ያልታደገች ጎልን ቢያስቆጥርም ጨዋታው በመቻል 3ለ1 አሸናፊነት ተቋጭቷል።

ኢትዮጵያ መድን 1-1 ሲዳማ ቡና

ሲዳማ ቡናዎች የተሻለውን አጀማመር ባደረጉበት የመጀመሪያው አጋማሽ ወደ ጎል የቀረቡት እነርሱ ቢመስልም ጎል ግን ቀድመው አስተናግደዋል። 19ኛው ደቂቃ ላይ ረመዳን የሱፍ ከግራ ራሱ ያስጀመረውን ኳስ ዳዊት አውላቸው ለወገኔ አቀብሎት አማካይ ወደ ጎል ሲመታ ረመዳን እግሩ ስር የገባችለትን ኳስ መሬት ለመሬት አክርሮ መቶ መረብ ላይ በማሳረፍ ቡድኑን ቀዳሚ አድርጓል። በጎል መቀደማቸው ወደ አቻነት እንዲመጡ የበለጠውን እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ያስቻላቸው ሲዳማ ቡናዎች 30ኛው ደቂቃ ላይ ብርሀኑ በቀለ ከፍቅረየሱስ ተወልደብርሃን ያገኘውን ኳስ በድንቅ አጨራረስ አስቆጥሮ ጨዋታው 1ለ1 ማድረግ ችሏል።

ከዕረፍት መልስ ሲዳማ ቡናዎች መሪነታቸውን ለማጠናከር ለተጨማሪ ጎሎች በድግግሞሽ ጫናን ሲያሳድሩ መመልከት ብንችልም 90+2 ላይ ሀብታሙ ታደሠን በሁለት ቢጫ ማጣታቸው የአጋማሹ ልዩነት ፈጣሪዋ ክስተት ሆና ጨዋታው በመጨረሻም 1ለ1 ተቋጭቷል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
Previous Article ቡናማዎቹ ከአሰልጣኝ አብይ ዘላለም ጋር ተለያዩ
Next Article አሰልጣኝ ፍሬው ሃ/ገብርኤል ወደ ኢትዮጵያ ቡና…!

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ

የኢትዮጵያ ሴቶች ኘሪሜየር ሊግ  የዋንጫ ጨዋታ  በቀጥታ /LIVESCORE/

hatricksport team By hatricksport team 9 years ago
ተስፋዬ አለባቸው ወደ ሀድያ አምርቷል
” ዘንድሮ እኔን እና ኢትዮ ኤሌክትሪክን ወደ ሚገባን ሊግ ማሳደግ ነው ዕቅዴ ” ፀጋ ደርቤ /ኢትዮ-ኤሌክትሪክ /
ባህርዳር ከተማ የፍቃዱ ወርቁን ውል አራዘመ
16ኛው የአዲስ አበባ ሲቲ ካፕ ዋንጫ የፊታችን ቅዳሜ ኢትዮጵያ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ቅ/ጊዮርጊስ ከመቻል በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?