ወጣቱ አሰልጣኝ አብይ ካሳሁን ባስገባው የመልቀቂያ ደብዳቤ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ተለያየ።
ትላንት በድሬዳዋ ከተማ የ2ለ1 ሽንፈትን ያስተናገደው ኢትዮጵያ ቡና በያዝነው የውድድር ዘመን ክለቡን በዋና አሰልጣኝነት ሲመሩ ከነበሩት አሰልጣኝ አብይ ካሳሁን ጋር በስምምነት ተለያየ።
የአሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ ረዳት በመሆን ባለፈው አመት አጋማሽ ዋናውን ቡድን የቀላቀለው ወጣቱ አሰልጣኝ በዋና አሰልጣኝነት ለአንድ አመት ቡድኑን ዘንድሮ በመረከብ በፕሪምየር ሊጉ ቆይታን ሲያደርግ የነበረ ቢሆንም ቡድኑ ካደረጋቸው አስራ አንድ ጨዋታዎች በአምስቱ ተሸንፎ ፣ ሦስቱን አሸንፎ ፣ በሦስቱ አቻ ወጥቶ አስራ ሁለት ነጥብ ብቻ ይዞ በደረጃ ሰንጠረዡ 13ኛ ላይ የተቀመጠ ሲሆን በውጤቱ እጦቱ ከቀናት በፊት ለአሰልጣኙ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ የተሰጠው አሰልጣኙ በተደጋጋሚ በደጋፊው ተቃውሞን እያስተናገደ ሲያስናግድ ሰንብቶ በዛሬው ዕለት አሰልጣኙ ባስገባው የመልቀቂያ ደብዳቤ ከቡድኑ ጋር መለያየቱ ታውቋል።



