By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኤልፓ እና ብርቱካናማዎቹ ወሳኝ ድል አስመዝገበዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የዲሲፕሊን ውሳኔዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግኢትዮጵያ ቡናዜናዎችኢትዮ-ኤሌክትሪክየጨዋታ ዘገባሽረ ምድረገነት

ኤልፓ እና ብርቱካናማዎቹ ወሳኝ ድል አስመዝገበዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 months ago
Share
SHARE

ድሬዳዋ ከተማ ከአምስት ፤ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ደግሞ ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ አሸንፈዋል

የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ11ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ሲደረጉ አዲስ አበባ ላይ በተደረጉት ጨዋታዎች ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ድሬዳዋ ከተማ ጣፋጭ ድሎችን አሳክተዋል።

ከቀን 07:00 ጀምሮ በተደረገው ቀዳሚው ጨዋታ ምድረ ገነት ሽረን የገጠመው የዘሪሁን ሸንገታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ የማታ ማታ ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል።

ቀዝቀዝ ያለ የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የታየበት ጨዋታው ይህ ነው ሊባል የሚችል የግብ ጠባቂዎቹን የፈተነ የግብ ሙከራ ያላስመለከተ ነበር።

- ማሰታውቂያ -

ነገር ግን የጨዋታው መጠናቀቂያ የፊሽካ ድምፅ በሚጠበቅበት ደቂቃ ላይ ኢትዮ ኤሌክትሪኮች ጣፋጭ ሶስት ነጥቦች ያሳኩበትን ጎል አስቆጥረዋል።

ግቡ የተቆጠረው በ90+4 ደቂቃ ላይ ሲሆን ግብ አስቆጣሪው ደግሞ አቤል ሀብታሙ ነው።

ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ነጥቡን 20 አድርሷል።

በ12ኛው ሳምንት ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከፋሲል ከነማ እንዲሁም ምድረ ገነት ሽረ ከአዳማ ከተማ ይጫወታሉ።

ከ10:00 ጀምሮ በተደረገው የኢትዮጵያ ቡና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ ደግሞ ድሬዳዋ ከተማ ከመመራት ተነስቶ 2 ለ 1 አሸንፏል።

ኢትዮጵያ ቡና የተሻለ በነበረበት የመጀመሪያ አጋማሽ የድሬዳዋ ከተማን የኳስ ምስረታ በጫና በማቋረጥ የግብ ዕድሎችን ጭምር መፍጠር ችለዋል።

በ24ኛው ደቂቃ ላይ ዘላለም አባተ ከቀኝ የሳጥኑ አቅጣጫ የተቀነሰለትን ኳስ አስቆጠረው ተብሎ ሲጠበቅ ኳሱን ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

ከሁለት ደቂቃዎች በኋላ አቤል ነጋሽ የቡናማዎቹን ተከላካዮች መዘናጋት ተከትሎ ያገኘውን ዕድል መጠቀም አልቻለም።

ጨዋታው 30ኛው ደቂቃ ላይ ሲደርስ ግን በቡናማዎቹ በኩል የመጀመሪያው ግብ ተቆጥሯል።

አቡበከር አዳሙ በሳጥኑ የግራ ሳጥን መግቢያ ላይ ያገኘውን ኳስ በጠንካራ ምት ወደ ግብ በመላክ ኢትዮጵያ ቡናን መሪ ያደረገውን ግብ ማስቆጠር ችሏል።

የቡናማዎቹ ብልጫ ቀጥሎ በታየባቸው ቀጣዮቹ የመጀመሪያ አጋማሽ ደቂቃዎች ላይም በተደጋጋሚ ወደ ድሬዳዋ ከተማ የግብ ክልል መድረስ ችለው የነበረ ቢሆንም ሌላ ግብ ማከል አልቻሉም።

በድሬዳዋ ከተማ በኩል ግሩም መኩሪያ እና አቤል ነጋሽ ያደረጓቸው ሙከራዎች በአጋማሹ የታዩ የግብ ዕድሎቻቸው ነበሩ።

ድሬዳዋ ከተማዎች ተሽለው በታዩበት የሁለተኛው አጋማሽ በተለይም በቀኝ መስመር ያደረጓቸው ተደጋጋሚ የግብ ዕድል መፍጠር ሙከራዎች ፍሬን አፍርተዋል።

በአጋማሹ ቀዳሚ የነበረው ሙከራ አቡበከር አዳሙ በ54ኛው ደቂቃ ያደረገው ሲሆን አብይ ካሳዬ ግብ ከመሆን አድኖታል።

በድሬዳዋ ከተማ በኩል ያሬድ ታደሰ በ58ኛው ደቂቃ ላይ ከመስመር የተሻገረን ኳስ ለመጠቀም ያደረገው ጥሩት ለድሬዳዋ ከተማዎች አስቆጪ አጋጣሚ ነበር።

ተደጋጋሚ ጫና የበረታባቸው ቡናማዎቹ የኋላ ክፍላቸውን ቁጥር በመጨመር የግብ ክልላቸውን ለመጠበቅ ያደረጉት ውሳኔ የኋላ ኋላ ዋጋ ያስከፈላቸው ሆኗል።

በ77ኛው ደቂቃ ላይ ተከላካዩ ጀሚል ያዕቆብ በሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ይዞ የገባውን ኳስ አክርሮ በመምታት ድሬደዋ ከተማን አቻ አድርጓል።

ከግቡ መቆጠር አስር ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ መሐመድኑር ናስር ከተመሳሳይ አቅጣጫ የተነሳውን ኳስ በእንደሻው እሸቴ መረብ ላይ አሳርፏል።

89ኛው ደቂቃ ላይ በፍቃዱ አለማየሁ የድሬዳዋ ግብ ጠባቂ አብይ ካሳዬን ደርቦ ያደረገው ሙከራ ለጥቂት ሳይቆጠር ቀርቷል።

በተጨማሪ ደቂቃዎች ላይ ድሬዳዋ ከተማዎች 3ኛ ግብ ማስቆጠር የሚችሉበትን ዕድል ቢያገኙም አብዲሳ ጀማል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።

ድሬዳዋ ከተማ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን 16 ማድረስ ችሏል።

በ12ኛው ሳምንት ኢትዮጵያ ቡና ከመቻል እንዲሁም ድሬዳዋ ከተማ ከነገሌ አርሲ ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

አርባምንጭ ከተማ ጋናዊ አጥቂ አስፈረመ

የ22ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article መቐለ እና ሀድያ ሆሳዕና ወሳኝ ድል አሳክተዋል
Next Article ሀዋሳ ተከታታይ ሁለተኛ ድልን ሲያሳካ ፈረሰኞቹ እና ሀምራዊ ለባሾቹ ነጥብ ተጋርተዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎችባህርዳር ከተማ

የጣና ሞገዶቹ ከአዲሱ አሰልጣኛቸው ጋር በይፋ ተፈራርመዋል!!

Ermias Misganaw By Ermias Misganaw 5 years ago
ድሬዳዋ ከተማ “ተበድያለሁ” ሲል ምሬቱን አሰምቷል።
የሊጉ ኮኮብ ጎል አስቆጣሪ ወደ መቻል ለመምራት ተስማማች
​በኦሮሚያ ዋንጫ ሰበታ ከተማ እና ጅማ አባቡና ለፍፃሜ ደረሡ
አዲስአበባ ከተማ አስራት አባተን ዋና አሳልጣኝ አድርጎ ቀጥሯል 
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?