By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ሪፖርት | የዛሬ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ጨዋታዎች ሀዋሳ እና ፋሲልን ባለ ድል አድርገዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ፋሲል ከነማየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግወላይታ ድቻዜናዎችሀዋሳ ከተማሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባ

ሪፖርት | የዛሬ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ጨዋታዎች ሀዋሳ እና ፋሲልን ባለ ድል አድርገዋል

fitsum Wadu
fitsum Wadu 4 months ago
Share
SHARE

በበርካታ ደጋፊዎች ፊት የተደረገው የሦስተኛው ሳምንት የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሁለት ጨዋታዎች በሐይቆቹ እና አፄዎቹ አሸናፊነት ተቋጭቷል።

ሀዋሳ ከተማ 2-1 ወላይታ ድቻ

የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን የመጀመሪያ ጨዋታ በበርካታ ደጋፊዎች መካከል የተደረገ ሲሆን በመጀመሪያው አጋማሽ ተመጣጣኝ መልክ የነበረው እንቅስቃሴዎች በይበልጥ የተመለከትንበት ሲሆን 14ኛው ደቂቃ ላይም በፈጣን ሽግግር ለመጫወት ጥረት ያደረጉት የጦና ንቦቹ መሪ መሆን የቻሉበት ነበር። ያሬድ ዳርዛ ከግራ መስመር አቅጣጫ ወደ ውስጥ ያሻገረውን ኳስ ካርሎስ ወደ ጎልነት ለውጦ ቡድኑን ቀዳሚ አድርጓል። ጎልን ካስተናገዱ በኋላ ቶሎ ቶሎ የተጋጣሚያቸውን ሦስተኛው የሜዳ ክፍልን መጎብኘትን የጀመሩት ሐይቆቹ 26ኛው ደቂቃ በጥሩ ቅብብል ቢኒያም በላይ ከሽመልስ በቀለ ያገኘውን መሬት ለመሬት ሲያቀብለው ወደ ግራ ኳስን ገፍቶ ሳጥን የገባው ወጣቱ ያሬድ ብሩክ በድንቅ አጨራረስ ቢኒያም ገነቱ መረብ አሳርፎ ቡድኑን አቻ አድርጓል። ወደ አቻነት መምጣታቸው በራስ መተማመናቸውን ከፍ ያደረገላቸው ሀዋሳ ከተማዎች 37ኛው ደቂቃ ከእጅ ውርወራ የአብስራ ደግፌ የሰጠውን ኳስ ሳጥን ጠርዝ ሆኖ ያገኘው ያሬድ ብሩክ እጅግ አስደናቂ ጎልን በድጋሚ ቢኒያም ገነቱ የኋላ መረቡ ላይ በማሳረፍ ቡድኑን ከተመሪነት ወደ መሪነት አሸጋግሯል።

ከዕረፍት ሲመለስ የቀጠለው እና በይበልጥ የሚቆራረጡ ኳሶች የተበራከቱበት አጋማሽ ሀዋሳ ከተማዎች ወደ ኋላ በማፈግፈግ ያስቆጠሯቸውን ጎሎች በማስጠበቅ በጥቂቱ ግን በመልሶ ማጥቃት ለመጫወት ጥረት ያደረጉበት ቢሆንም የአሰልጣኝ ገብረክርስቶስ ቢራራው ወላይታ ድቻ ግን የተጫዋቾች ቅያሪን በማድረግ ጫናዎች በሚያሳድሩ ረጃጅም ኳሶቻቸው ብልጫውን መያዝ ቢችሉም ሳይሳካላቸው ጨዋታው በሀዋሳ ከተማ 2ለ1 የበላይነት ተጠናቋል።

- ማሰታውቂያ -

ፋሲል ከነማ 1-0 ሲዳማ ቡና

ሌላኛው ምሽቱን በርካታ ደጋፊዎች የታደሙበት የፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና ጨዋታ የቡናማዎች የኳስ ንክኪ ብልጫ የአፄዎቹ ደግሞ የጥንቃቄ አጨዋወትን በሙሉ የጨዋታ ደቂቃው ያስዋልንበት ነበር ማለት ይቻላል። ከጅምሩ ከመስመር መነሳትን መርጠው የበላይነትን በሜዳቸው ሲያሳዩ የነበሩት ሲዳማ ቡናዎች 14ኛው ደቂቃ ላይ በቅብብል ስህተት ጎልን ለማስተናገድ ተገደዋል። ያሬድ ባዬ ከአስቻለው ሙሴ ያገኘውን ኳስ ወደ ኋላ ለዮሴፍ ዮሐንስ ሲያቀብለው ከጀርባው የነበረው በረከት ግዛው በጥሩ አጨራረስ በሦስት ጨዋታ ሦስተኛ ጎሉን በማስቆጠር ፋሲልን መሪ በማድረግ አጋማሹ ተገባዷል።

ከዕረፍት በፊትም የበላይ የነበሩት እና በሁለተኛውም አጋማሽ ከቆሙበት የቀጠሉት ሲዳማ ቡናዎች የተጫዋች ቅያሪን በማድረግ ቢያንስ ወደ አቻነት ለመምጣት ከየትኛውም አቅጣጫ ሳጥን በሚጣሉ የዐየር ላይ እና የመሬት መሬት ማቀበሎችን ቶሎ ቶሎ ቢያሳዩንም ከነበራቸው ጥድፊያዎች አኳያ የግብ ዘቡን ሞይስ ፓዎቴን ድንቅ ብቃት ተገዳድረው ጎሉን ማስቆጠር ግን አልቻሉም። በመከላከል ይጠመዱ እንጂ በመልሶ ማጥቃት ተጨማሪ ጎል ሊሆን የሚችሉ አጋጣሚዎችን ያገኙ የነበሩት አፄዎቹ በመጨረሻም ተሳከሰቶላቸው 1ለ0 አሸናፊ ሆነው ወጥተዋል። ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በተደጋጋሚ ከአራተኛው ዳኛው አዳነ ወርቁ ጋር በጨዋታ እና ከጨዋታ በኋላ ጭቅጭቅ ሲፈጥር የነበረው ደግፌ ዓለሙ በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ሊወገድ ችሏል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
Previous Article ፈረሰኞቹ በአቤል ያለው ግብ አሸንፈዋል
Next Article ደሴ ከተማ አጥቂ አስፈረመ !

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎችሀዋሳ ከተማፋሲል ከተማሰበር ዜና

ፋሲል ከተማ አሰልጣኝ ውበቱ አባተን አስፈርሟል

hatricksport team By hatricksport team 8 years ago
ሻሸመኔ ከተማ ከዝውውር ታገደ
“በአሰልጣኝ ውበቱ ስር ከዳዊትና መስዑድ ጎን በመጫወቴ ደስተኛ ነኝ”ታደለ መንገሻ /ሰበታ ከተማ/
ቡናማዎቹ ተጫዋች ለማስፈረም ተስማሙ !
የጨዋታ ዘገባ | ቅዱስ ጊዮርጊስ መሪነቱን አጠናክሮ ያስቀጠለበትን ዉጤት አስመዝግቧል።
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?