በትግራይ ደርቢ የተገናኙት ሽረ ምድረገነት እና መቐለ 70 እንደርታ ያገረጉት መርሀግብር ሽረዎች በዳንኤል ዳርጌ ብቸኛ ጎል አሸናፊ ሆነዋል።
ተመጣጣኝ እንቅስቃሴዎች የነበሩት ነገር ግን በሙከራዎች ብዙም መድመቅ ያልቻለው ጨዋታ በመጀመሪያው አጋማሽ በተወሰነ መልኩ የመጨረሻው ሜዳ ላይ ኮስታራ ለመሆን ጥረት ሲያደርጉ የሚስተዋሉት ሽረዎች ተካልኝ ደጀኔ ከግራ መስመር ያሻገረውን ኳስ ሽመክት ጉግሳ አመቻችቾ አቀብሎት ዳንኤል ዳርጌ በጥሩ አጨራረስ ጎል አድርጎታል። ጎል ካስተናገዱ በኋላ በፈጣን ሽግግር ከመስመር መነሳትን መርጠው የተጫወቱት መቐለዎች ቦና ዓሊ ከብርሀኑ አዳሙ ያገኘውን ኳስ በቀላሉ ካመከናት በኋላ አጋማሹ በሽረ ምድረገነት 1ለ0 መሪነት ተጋምሷል።
ከዕረፍት መልስ በቀጠለው ጨዋታ ሽረዎች በይበልጥ ወደ ኋላ በማፈግፈግ ያስቆጠሯትን ጎል ለማስጠበቅ ጥረት ሲያደርጉ በአንፃሩ መቐለ 70 እንደርታ በአዲስ ጉልበት ተጫዋቾችን ቀይሮ በማስገባት ጫናዎችን ማሳደር ቢችሉም ከጎል ጋር መገናኘቱ ግን ከብዷቸው ተመልክተናል። በተለይ ኪቲካ ጀማ ለፍፁም ሰቶት አማካዩ ሞክሮ የግብ ዘቡ ሪችሞንድ አዩ ያመከተነበት ስንታየሁ መንግስቱ በደካማ እግሩ መቶ ሪችሞንድ አዩ ሲያምክንበት ብርሀኑ አዳሙም ካደረጋት እና ሪችሞንድ ለሦስተኛ ጊዜ ካዳናት ኳስ በኋላ ጥቅጥቅ ባለ መከላከያ ውስጥ የተጠመዱት ሽረዎች ተሳክቶላቸው አሸንፈው ወጥዋል።



