By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ባህርዳር ከተማ ድል ሲቀናው ሻምፒዮኑ ዓመቱን በአቻ ጀምሯል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችባህርዳር ከተማአዳማ ከተማሀዲያ ሆሳዕናየጨዋታ ዘገባኢትዮጵያ መድህን

ባህርዳር ከተማ ድል ሲቀናው ሻምፒዮኑ ዓመቱን በአቻ ጀምሯል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 5 months ago
Share
SHARE

የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት የመጨረሻ ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ሲደረጉ የአዲስ አበባ ስታድየም ሁለት ጨዋታዎችን አሰትናግዷል።

ከቀን 7:00 ጀምሮ የተደረገው የኢትዮጵያ መድን እና አዳማ ከተማ ተጠባቂ ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት ተጠናቋል።

ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ በታየበት የመጀመሪያው አጋማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በሁለቱም በኩል አስቀድሞ ግብ ለማስቆጠር ጥረቶች ተደርገዋል።

ምንም እንኳን በሁለቱም በኩል ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል ለመድረስ ጥረቶች ቢኖሩም በግብ ሙከራዎችን የታጀቡ አልነበሩም።

- ማሰታውቂያ -

16ኛው ደቂቃ ላይ በኢትዮጵያ መድን በኩል ረመዳን የሱፍ በቀኝ መስመር የደረሰውን ኳስ በጥሩ ሁኔታ ተቆጣጥሮ ወደ ግብ ቢልከውም የግቡ ቋሚ መልሶበታል።

በአዳማ ከተማ በኩል ደግሞ 38ኛው ደቂቃ ላይ ቢንያም አይተን ከአህመድ ሁሴን የተቀበለውን ኳስ ሞክሮ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቶበታል።

ከመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ እንቅስቃሴ ከግብ ሙከራዎች እና ሽኩቻዎች ጋር ባስመለከተን የሁለተኛው አጋማሽ ጥሩ እንቅስቃሴ ታይቷል።

በ48ኛው ደቂቃ ላይ ዳዋ ሆጤሳ በሳጥኑ የቅርብ ርቀት ያገኘውን የቅጣት ምት ሞክሮ ለጥቂት ወጥቶበታል።

በሁለቱም ቡድኖች በኩል ቀዳሚውን ግብ ለማድረግ የሚደረጉት ጥረቶች በቀላሉ የተጋጣሚ ሳጥን ገብተው የግብ ዕድል ለመፍጠር አልቻሉም።

በዚህም በተለይም ከሳጥን ውጪ የሚደረጉ መከራዎች በተደጋጋሚ በጨዋታው ተስተውለዋል።

በቀጣይም በ56ኛው እና 60ኛው ደቂቃዎች ላይ ዳዋ ሆጤሳ እና አህመድ ሁሴን ከሳጥን ውጪ ጠንካራ የግብ ሙከራዎችን አድርገዋል።

በኢትዮጵያ መድን በኩል ደግሞ ወገኔ ገዛኸኝ ሁለት ጠንከር ያሉ የግብ ሙከራዎችን ከሳጥን ውጪ ቢያደረግም በግብ ጠባቂው አላዛር ማርቆስ ተይዞበታል።

በጨዋታው የአዳማ ከተማው አምበል ሀይደር ሸረፋ የቀድሞ ቡድኑን በገጠመበት ጨዋታ በበረከት ካሌብ ላይ በሰራው ጥፋት በሁለተኛ የቢጫ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

በመጨረሻም ጨዋታው ግብ ሳይቆጠርበት የተጠናቀቀ የመጀመሪያው ሳምንት ብቸኛ ጨዋታ ሆኗል።

ከ10:00 ጀምሮ የተደረገው የባህርዳር ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ በጣና ሞገዶቹ የ3 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።

በጨዋታው ባህርዳር ከተማዎች መሪ ለመሆን የፈጀባቸው ሰባት ያህል ደቂቃዎች ብቻ ናቸው።

በተጠቀሰው ደቂቃ ላይ ከማዕዘን የተሻገረውን ኳስ ክንዱ ባየልኝ በግንባር በመግጨት ከመረብ ላይ አሳርፎታል።

በቀጣዮቹ ደቂቃዎች በሁለቱም በኩል በፈጣን የጨዋታ ሒደቶች ግቦችን ለማስቆጠር ጥረቶች ተደርገዋል።

በነብሮቹ በኩል ተመስገን ብርሀኑ እና ሔኖክ አርፊቹ ያደረጓቸው እና በፔፔ ሰይዶ ተሞክረው የተያዙት ኳሶቹ በቡድኑ በኩል የተደረጉ ኢላማቸውን የጠበቁ የመጀመሪያው አጋማሽ ሙከራ ናቸው።

በባህርዳር ከተማ በኩልም በተደጋጋሚ ወደ ሀድያ ሆሳዕና ሳጥን መድረስ ቢችሉም ግብ ጠባቂውን የፈተነ ሙከራ ማድረግ አልቻሉም።

በሁለተኛው አጋማሽ ባህርዳር ከተማዎች ሁለተኛውን ግብ ለማስቆጠር ከሁለት ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ነበር ያስፈለጋቸው።

የቡድኑ አዲስ ፈራሚ አማኑኤል ገብረሚካኤል ከወንድወሰን በለጠ ከሳጥኑ የቀኝ አቅጣጫ ተልኮ የሀድያ ሆሳዕናው ግብ ጠባቂ ያሬድ በቀለ በቀላሉ ለመቆጣጠር ሳይችል በመቅረቱ ኳሱን ያገኘው አማኑኤል ኳስ እና መረበንን አገናኝቷል።

የ2 ለ 0 መመራትን ለመቀልበስ የተለያዩ ቅያሪዎችን በማድረግ ጨዋታውን የቀጠሉት ሀድያ ሆሳዕናዎች በጫላ ተሺታ አማካይነት ግብ አስቆጥረው ወደ ጨዋታው ተመልሰዋል።

ባህርዳር ከተማ የሶስተኛ ሀድያ ሆሳዕናዎች ደግሞ የአቻነት ግብ ፍለጋን ሲያደርጉት ከነበረው ጥረት ባለፈ ከባባድ ጥፋቶችም በጨዋታው ተስተውለዋል።

በተለይም ኤልያስ አህመድ በክንዱ ባየልኝ ላይ የሰራው አደገኛ ጥፋት ተጫዋቹን የቀጥታ ቀይ ካርድ ሰለባ አድርጎታል።

የውጤትም የተጫዋች ቁጥርም ብልጫ የተወሰደባቸው ነብሮቹ በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች ላይ ግብ ለማግኘት ብልጫን ወስደው ቢጥሩም በተቃራኒው ግብ አስተናግደዋል።

ተቀይሮ የገባው ሴዝ ኦሴ በ78ኛው ደቂቃ ላይ ከሳጥን ውጪ አክርሮ የመታው ኳስ የግቡን ቋሚ ገጭቶ ከመረብ ላይ አርፏል።

በመጨረሻም ባህርዳር ከተማ በ3 ለ 1 ውጤት በጨዋታው አሸናፊ ሆኗል።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ሪፖርት | የናይጄሪያዊው አማካይ አስደናቂ ጎል መቻልን ባለ ድል አድርጓል
Next Article ሪፖርት | ሽረ ምድረገነት ሊጉን በድል ጀምሯል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዋልያዎቹየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንዜናዎች

ዋልያዎቹ አይቮሪኮስት ላይ ወሳኝ ድል ተቀዳጁ

ዳዊት ብርሀነ By ዳዊት ብርሀነ 6 years ago
ሸገር ሲቲ ግብ ጠባቂ አስፈረመ
​በአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ሲቀናው መከላከያ ከ ኤሌትሪክ አቻ ተለያይቷል
ቅዱስ ጊዮርጊስ የፊት መስመር አጥቂ አስፈርመዋል!
ኢንተርናሽናል ዳኛ ባምላክ ተሰማ ቅሬታ ቀረበበት !
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?