የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታድየም ተደርጎ የሊጉ የሁለት ጊዜ ሻምፒዮን ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሸገር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።
በጨዋታው የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ አዲስ አዳጊው ሸገር ከተማ በፍጥነት ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል በመድረስ የተሻለው ቡድን ነበር።
በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ በሚመራው ቡድን በኩል የግብ ዕድሎችን በነዚህ የመጀመሪያ ደቂቃዎች ላይ ለመፍጠር ጥረቶች ቢኖሩም ኢላማቸውን የጠበቁ አልነበሩም።
በሸገር ከተማ በኩል በተለይም በመስመሮች በኩል የማጥቃት ፍላጎቶች በተደጋጋሚ ተስተውለዋል።
- ማሰታውቂያ -

በኤልፓ በኩል ረጃጅም ኳሶችን ወደ ሸገር ከተማ የግብ ክልል በማድረስ የማጥቃት ሒደቶችን ለመፍጠር የሚላኩት ኳሶች በቀላሉ በሸገር ከተማ ተጫዋቾች ይነጠቁ ነበር።
ደቂቃዎች በጨመሩ ቁጥር መሀል ላይ መነጣጠቆች በበዙት ጨዋታው በሁለቱም በኩል ለግብ የቀረቡ ሙከራዎችን ለማድረግ በርካታ ደቂቃዎች ለመጠበቅ ተገደዋል።
በሸገር ከተማ በኩለ በ36ኛው ደቂቃ ላይ አንተነህ ተፈራ ከአሸናፊ ጥሩነህ የነጠቀውን ኳስ አጥቂው ያሬድ መኮንን አግኝቶ ነፃ ለነበረው አሚር አብዶ ቢያቀብለውም አሚር አብዶ ከግቡ አናት በላይ ኳሷን ልኳታል።
በኢትዮ ኤሌክትሪክ በኩል ደግሞ እዮብ ገብረማርያም በ45ኛው ደቂቃ ላይ ከሳጥን ውጪ አክርሮ በመምታት ያደረገው ድንቅ ሙከራ በግብ ጠባቂው ምንተስኖት የግሌ ተይዟል።
ሁለተኛው አጋማሽ የጨዋታው ክፍለ ጊዜ በሁለቱም በኩል በርከት ያሉ የግብ ሙከራዎች በሁለቱም ቡድኖች በኩል የታዩበት ነበር።
በሁለተኛው አጋማሽ በጥሩ የማጥቃት እንቅስቃሴ የጀመሩት ሸገር ከተማዎች በ49ኛው ደቂቃ ላይ አንተነህ ተፈራ ይዞት በገባው ኳስ ጠንካራ የግብ ሙከራ ቢያደርጉም በረኛው መልሶታል።
በድጋሚ ከማዕዘን የተሻገረውን ኳስ አሚር አብዶ ሲያሻግር ያገኘው አንተነህ ተፈራ በግንባር የመታው ኳስ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።
በ55ኛ ደቂቃ ግን ሸገር ከተማ ግብ አስቆጥሯል። ከርቀት የተመታውን ኳስ ግብ ጠባቂው መቆጣጠር ሲያቅተው ያገኘው አብነት ተስፋዬ ግብ አስቆጥሯል።

ከደቂቃዎች በኋላ ሀሰን ሁሴን ከግራ መስመር ተነስቶ ወደ ሳጥን በመግባት አሪፍ ሙከራ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ኳሱ ለጥቂት ወደ ውጪ ወጥቷል።
በሸገር ከተማ በኩልም ከሳጥን ውጪ ጠንካራ የግብ ሙከራ የተደረገ ሲሆን አሸብር ተስፋዬ በጥሩ ብቃት ተቆጣጥሮታል።
በአጋማሹ ይበልጥ ወደ ተጋጣሚ የግብ ክልል መድረስ የቻሉት ኤልፓዎች በ62ኛው ደቂቃ ላይ በቢንያም በቀለ አማካይነት ከቆመ ኳስ የተደገረ ሙከራን ግብ ጠባቂው ምንተስኖት የግሌ ከመረብ አድኖታል።
በ71ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ እዮብ ገብረማርያም ካልተጠበቀ አቅጣጫ ያደረገው ጠንካራ የግብ ሙከራ በድጋሚ በግብ ዘቡ ምንተስኖት ተይዟል።
ኢትዮ ኤሌክትሪክ ተጨማሪ ግብ ለማግኘት ጥረታቸውን ሲቀጥሉ ሸገር ከተማዎች በተለይም ከመስመር በሚነሱ ኳሶች አቻ ለመሆን ጥረዋል።
በ90ኛው ደቂቃ ላይ ሸገር ከተማዎች ጥሩ ዕድል አግኝተው የነበረ ቢሆንም ሊጠቀሙበት አልቻሉም።
አንተነህ ተፈራ ከግብ ጠባቂው ጋር ተገናኘረቶ ያደረገው ሙከራ ሲመለስ ዳግም ራሱ እና ሌሎች ሁለት ተጫዋቾች ለማግኘት ቢጥሩም ያሬድ የማነ ደርሶ አውጥቶታል።
በመጨረሻም በአሰልጣኝ ዘሪሁን ሸንገታ የሚመራው ኢትዮ ኤሌክትሪክ 1 ለ 0 በማሸነፍ የውድድር ዘመኑን በድል ጀምሯል።
በሁለተኛው ሳምንት ጨዋታዎች ጥቅምት 13(ሀሙስ) ሸገር ከተማ ከአዳማ ከተማ እንዲሁም ጥቅምት 14(አርብ) ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከደግሞ ከሀድያ ሆሳዕና ይጫወታሉ።


