By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ሲዳማ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ አሸንፈዋል
Share
Notification Show More
Latest News
ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡና የጨዋታ ዘገባ መቻል የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ወልዋሎ
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሲዳማ ቡናየጨዋታ ዘገባወላይታ ድቻዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስሀዋሳ ከተማባህርዳር ከተማኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ ሲዳማ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ አሸንፈዋል

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 11 months ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት የሁለተኛ ቀን ሶስት ጨዋታዎች ዛሬ ከረፋድ እስከ ምሽት ድረስ ተደርገዋል።

ከረፋድ 3:30 ጀምሮ በተደረገው የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸንፏል።

የሳይመን ፒተር የ21ኛ ደቂቃ ግብ የአምናውን ሻምፒዮን አሸናፊ ለማድረግ በቂ ነበር።

ከቅጣት ምት የተሻገረውን ኳስ ተመስገን ዮሐንስ ከግቡ ሲያርቅ ያገኘው ጋናዊው አጥቂ በቀጥታ በመምታት በ21ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል።

- ማሰታውቂያ -

በሁለተኛው አጋማሽ ተጭነው በመጫወት የግብ ዕድሎችን መፍጠር የቻሉት ቅዱስ ጊዮርጊሶች ኳስ እና መረብን ማገናኘት ሳይችሉ ቀርተዋል።

በሊጉ በስኬታማነት ቀዳሚ የሆነው ቅዱስ ጊዮርጊስ የውድድር ዘመኑ ስምንተኛ ሽንፈቱ ሲሆን ፤ ከድል ከተራራቀ ደግሞ ሰባተኛ ተከታታይ ጨዋታው ሆኖ ተመዝግቧል።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነጥቡን 35 ማድረሱን ተከትሎ በጊዜያዊነት ወደ 5ኛ ደረጃ ከፍ ሲል ቅዱስ ጊዮርጊስ በበኩሉ በ31 ነጥቦች ወደ 11ኛ ደረጃ ዝቅ ብሏል።

በዕለቱ ሁለተኛ ጨዋታ ደግሞ ሲዳማ ቡና ባህርዳር ከተማን በፍቅረየሱስ ተክለብርሃን ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል።

በ24ኛው ደቂቃ ላይ አስቻለው ሙሴ ከማዕዘን ምት ያሻገረውን ኳስ ተጨራርፎ ያገኘው ፍቅረየሱስ ተክለብርሃን አክርሮ በመምታት አስቆጥሮታል።

አስር ቁጥር ለባሹ ባሳለፍነው ሳምንትም ቡድኑ ስሁል ሽረን ሲረታ የማሸነፊያውን ብቸኛ ግብ ማስቆጠሩ አይዘነጋም።

ውጤቱንም ተከትሎ ሲዳማ ቡና ነጥቡን 32 አድርሶ በጊዜያዊነት ደረጃውን ከ12ኛ ወደ 9ኛ አሻሽሏል።

ባህርዳር ከተማ በበኩሉ ከኢትዮጵያ መድን ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት የሚያጠብበትን ዕድል ሳይጠቀም ቀርቷል።

እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው ደጋፊዎች ስታድየም ተገኝተው በተከታተሉት እና ከአመሻሽ 12:00 ጀምሮ በተደረገው ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ወላይታ ድቻን በተመሳሳይ 1 ለ 0 አሸንፏል።

ለሀዋሳ ከተማ ኤርትራዊው ዓሊ ሱሌማን በ47ኛው ደቂቃ ላይ በረጅም የደረሰውን ኳስ በግሩም ሁኔታ በቮሊ በቀጥታ ወደ ግብ በመምታት ግሩም ግብ አስቆጥሯል።

ሀዋሳ ከተማ ያለውን ነጥብ 24 ቢያደርስም አሁንም ከወራጅ ቀጠናው መላቀቅ(15ኛ) አልቻለም።

ከሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎች በኋላ የተሸነፈው ወላይታ ድቻ በበኩሉ ነጥቡን 40 አድርሶ ከኢትዮጵያ መድን ያለውን ልዩነት ወደ 5 የሚያጠብበትን ዕድል ሳይጠቀም ቀርቷል።

ወላይታ ድቻ ከአምስት ጨዋታዎች በኋላ ግብ ያስተናገደበት ጨዋታ ሲሆን ግብ አስቆጣሪው ዓሊ ሱሌማን በበኩሉ 10ኛ የውድድር ዓመት ግቡ ሆኗል።

የሊጉ መርሐግብር በነገው ዕለትም ሲቀጥል ኢትዮጵያ ቡና ከፋሲል ከነማ እንዲሁም መቻል ከአርባምንጭ ከተማ ይጫወታሉ።

You Might Also Like

ወላይታ ድቻ የሊጉን መሪ አሸንፏል

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ብሩክ ባይሳ እና ፋሃድ አዚዝ የጨዋታ እገዳ ሲጣልባቸው እንዲሁም ከክለብ ኢትዮጵያ ቡና ቅጣት ተላልፎበታል
Next Article ኢትዮጵያ ቡና እና መቻል ተጋጣሚዎቻቸውን ረተዋል

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበርቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

ጎፈሬ ከባህርዳር ከተማ አስተዳደር የዳኞችና ታዛቢዎች ሙያ ማህበር ጋር የብራንድ ትጥቅ አቅርቦት ውል ተፈራረመ

hatricksport team By hatricksport team 4 years ago
ዳዊት ተፈራ ወደ ነገሌ አርሲ አመራ !!
ሴት አትሌቶቻችን የነገ(ቅዳሜ) የኦታዋ የ10ኪ.ሜ ውድድርን በድል እንደሚያጠናቅቁ ተናገሩ ፤
የ2010 ኢትዮጵያ ዋንጫ የ1ኛ ዙርና የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች በቀጥታ/ LIVESCORE/ ይከታተሉ
ሲዳማ ቡና የተከላካዩን ኮንትራት አራዝሟል!
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?