By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “ህልሜ የተሳካበት ቀን ነው” “ሻምፒዮን ስለመሆን ነው የማስበው” “የኢትዮጵያን ህዝብም ዲሲ ፓወርንም ማኩራት ነው የምፈልገው” ሎዛ አበራ ( ዲሲ ፓወር)
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ሎዛ አበራዜናዎች

“ህልሜ የተሳካበት ቀን ነው” “ሻምፒዮን ስለመሆን ነው የማስበው” “የኢትዮጵያን ህዝብም ዲሲ ፓወርንም ማኩራት ነው የምፈልገው” ሎዛ አበራ ( ዲሲ ፓወር)

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 2 years ago
Share
SHARE

“ህልሜ የተሳካበት ቀን ነው”

“ሻምፒዮን ስለመሆን ነው የማስበው”

“የኢትዮጵያን ህዝብም ዲሲ ፓወርንም ማኩራት ነው የምፈልገው”

ሎዛ አበራ ( ዲሲ ፓወር)

- ማሰታውቂያ -

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ዋና አምበል የሆነችው ሎዛ አበራ የአሜሪካ ሴቶች ሱፐር ሊግ ተሳታፊ የሆነውን ዲሲ ፓወርን መቀላቀሏን ቀደም ብለን መዘገባችን ይታወቃል።

ተጫዋቿ ፊርማዋን ካኖረች በኋላም በጋዜጣው መግለጫ ላይ ያካፈለችውን ሀሳብ ለዝውውሯ መሳካት ትልቁን ድርሻ የወሰደው የፊፋ ማች ኤጀንት እና አሰልጣኝ መዝሙረዳዊት መኩሪያ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አጋርቷል።

በጣም ደስ ብሎኛል ስትል ንግግሯን የጀመረችው ሎዛ አበራ ህልሜ የተሳካበት ቀን ነው ብላለች። አክላም እዚህ ደረጃ ለመድረስ ብዙ ፈተናዎች ስለመሻገሯ ተናግራለች።

“እዚህ ቦታ ለመቀመጥ በእግርኳስ ህይወቴ ውስጥ ብዙ ታግያለሁኝ። ዛሬ ደግሞ ህልሜ እውን ስለሆነ በጣም ደስ ብሎኛል።”

በቨርጂኒያ ማራውደርስ አስቀድማ ቆይታ ያደረገችው ሎዛ በክለቡ በነበራት ቆይታ በ11 ጨዋታዎች ላይ አስር ግቦችን አስቆጥራ ሰባት ደግሞ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችታ ማቀበሏን አስታውሳለች።

በዚህም በዲሲ ፓወር ክለብ ሰዎች አይን ውስጥ መግባቷን እና በተሰጣትም የሙከራ ጊዜ በሚገባ አቅሟን በማሳየቷ በክለቡ በቋሚነት ፊርማዋን ለማኖር እንዳገዛት ገልፃለች።

የዲሲ ፓወር እግርኳስ ክለብ በውድድር ዓመቱ የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች ድል ማስመዝገብ ያልቻለ ሲሆን የሎዛ ቡድኑም መቀላቀል የአጥቂ ክፍሉን እንደሚያጠናክረው አሰልጣኙ የሰጡትን አስተያየት አቅርበናል።

ሎዛም በዚህ ዓመት ከቡድኑ ጋር ዋንጫ ስለማሸነፍ እንደምታስብ በመግለጫው ላይ ተናግራለች።

“ከዲሲ ፓወር እግር ኳስ ክለብ ጋር በዘንድሮው ዓመት ትልቅ ስራ ሰርተን በሊጉ የተሻለ ውጤት ለማምጣት እና ሻምፒዮን ለመሆን ነው አንድ ላይ የማስበው።”

“ባለኝ አቅም ሁሉ ለቡድኑ የተሻለ ነገር ሰርቼ የኢትዮጵያን ህዝብም ዲሲ ፓወርንም ማኩራት ነው የምፈልገው።”

በክለቡ መቀመጫ በሆነው የDMV አካባቢ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የሚኖሩ መሆኑን ተከትሎም ለክለቡ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር በመጥቀስ ስታድየም በመገኘት ክለቡን እንዲደግፉ እና እሷንም እንዲያበረታቷት ጥሪ አቅርባለች።

“የኢትዮጵያ ህዝብ ኳስ የሚወድ ህዝብ ነው። ዲሲ ፓወር DMV አካባቢ በመቋቋሙ ደግሞ ብዙ ደጋፊዎች የዲሲ ፓወር ቤተሰብ እንደሚሆኑ አምናለሁ።”

“ይህ ዜና ይፋ ከሆነ በኋላ ብዙ ደጋፊዎች እንደምናገኝ እና ብዙዎች የዲሲ ፓወር ቤተሰብ እንደሚሆኑ እርግጠኛ ነኝ።”

ሎዛ አበራ አክላም ቡድኑ በመጪው መስከረም 2/2017 በሜዳው ኦዲ ፊልድ በሚያደርገው የዓመቱ የመጀመሪያ ጨዋታም እዛ አካባቢ ያለ ኢትዮጵያ ተገኝቶ ክለቡን እንዲደግፍ እና ከኔም ጎን እንዲሆን በዚሁ አጋጣሚ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ ብላለች።

ሎዛ እዚህ ለመድረሷ ያገዟትን ግለሰቦች ስም በመጥቀስ ጭምርም በመግለጫው ላይ አመስግናለች።

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article ሎዛ አበራ በአሜሪካ ሱፐር ሊግ ተሳታፊ ለሆነው ዲሲ ፓወር ፊርማዋን አኖረች
Next Article የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅጣት ተላለፈበት

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎችመቐለ 70 እንደርታ

የሊግ ኮሚቴው አመራሮች መስመሩን አልፈዋል፤ የክለባችንን መብት ተጋፍተዋል በዚህም አዝነናል” አቶ ሽፈራው (ተ/ኃይማኖት) የመቐለ 70 እንደርታ እግርኳስ ክለብ ዋና ስራ አስኪያጅ

ዮሴፍ ከፈለኝ By ዮሴፍ ከፈለኝ 6 years ago
የሀዋሳ ከተማ እና ሲዳማ ቡና የደርቢ ጨዋታ በአቻ ዉጤት ሲጠናቀቅ ፤ ኢትዮጵያ ቡናም ወሳኝ ድል አሳክቷል !!
“በ2016 የበጀት ዓመት ከ27 ሚልዮን ብር በላይ ጉድለት አጋጥሞኛል” የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
የ2012 ቶታል ግማሽ ማራቶን ትላንት በሀዋሳ ተካሄደ
የአቡበከር ናስርና የአርቢትር ሚካኤል ጠዓመ የአስጸያፊ ቃላት ጦርነት ዳኛውን ለቅጣት ዳረገ
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?