By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅጣት ተላለፈበት
Share
Notification Show More
Latest News
ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ
ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች
ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ዜናዎች የኢትዮጵያ እግርኳስ ዳኞች ማህበር
በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?
የዝውውር ዜናዎች ኢትዮጵያ ቡና ዜናዎች የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች አርባምንጭ ከተማ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅጣት ተላለፈበት

Habtamu Mitku
Habtamu Mitku 1 year ago
Share
SHARE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ የቀረበበትን ቅሬታ ሲመረምር የቆየው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን ኮሚቴ በክለቡ ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2016 የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 23ኛ ሳምንት መርሐግብር ከኢትዮጵያ ቡና 2 – 2 ከተለያየበት ጨዋታ በኋላ በጨዋታው በነበረው በየዳኝነት ውሳኔዎች ላይ ደስተኛ አለመሆኑን በማመላከት ቅሬታ አቅርቧል።

ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባቀረበው የቅሬታ ደብዳቤ ላይም የውድድሮች አመራር ዳኝነት የተወሰኑ ክለቦችን ወደ ክብር ኮርቻ ለማስቀመጥ በሚመስል መልኩ በውድድሮች ላይ ከሚመደቡ አንዳንድ ዳኞች መዋለ ንዋይ በመመደብ የአንድ ድርጅት ተወካይ ቡድን ድካምና ልፋት ውጤት የሚቀይሩ አነጋጋሪ የሆኑ ውሳኔ ሲወስኑ የታዩ በመሆኑ ለተፈፀመው የዳኝነት መዛባትም ሆነ በቀጣይ ጨዋታዎች ስለሚኖረው ፍታዊ ዳኝነት ዋስትና እንዲሰጠን በማለት ማቅረቡን የፌዴሬሽኑ መግለጫ አመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ደግሞ የቀረበው አቤቱታ ከተመለከተ በኋላ ግንቦት 04 ቀን 2016 ዓ.ም ባቀረበው አቤቱታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር በዳኞች ላይ የስም ማጥፋት ተግባር የፈፀመ በመሆኑ ጉዳዩ ተጣርቶ ተገቢው ውሳኔ ይሰጥልኝ በማለት ለዲስኘሊን ኮሚቴ አቅርቧል፡፡

- ማሰታውቂያ -

የዲስኘሊን ኮሚቴው የብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ያቀረበውን አቤቱታ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር ደርሶት መልስ እንዲሰጥበት በማዘዙ ክለቡ በብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ለቀረበው አቤቱታ ባቀረበው መልስ የጨዋታው ሂደት ከDSTV ማስረጃው እንዲታይልን እኛ ያቀረብነው የዳኝነት መዛባት እንጂ በዳኛ ሊመደብ የሚችል መዋለ ንዋይ ሊታሰብ የማይችል መሆኑን በመግለጽ በአጠቃላይ የብሔራዊ ዳኞች ያቀረበውን የስም ማጥፋት ተግባር እንዳልሆነ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር አቤቱታ በግልፅ ባስቀመጠው ሃሳብ እንደሚያመላክተው የውድድሩ ዳኞች የተወሰኑ ክለቦችን ወደ ክብር ኮርቻ ለማስቀመጥ በሚመስል መልኩ ውድድሮች ላይ የሚመደቡ አንዳንድ ዳኞች መዋዕለ ንዋይ በመመደብ የአንድን ድርጅት ተወካይ ቡድን የድካምና የልፋት ውጤት የሚቀይር አነጋጋሪ የሆኑ ውሳኔዎች ይወሰናሉ በማለት ገልጿል፡፡

ክለቡ ይህን ለማለት የቻለበት ምክንያትና ማስረጃ እንዲሁም መልስ እንዲሰጥበት ተጠይቆ ግንቦት 14 ቀን 2016 ዓ.ም ያቀረበው መልስ በጨዋታው ሂደት ዳኞች የፈፀሙት ጥፋት በDSTV ይታይልኝ፣ የዳኝነት መዛባት ማለቴ እንጂ በዳኛ ለመመደብ የሚችል መዋለ ንዋይ አይታሰብም በማለት ከነገሩ ለመሸሽ በማሰብ በሚመስል መልኩ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

በተጨማሪ በዲስኘሊን መመሪያ አንቀጽ 80/22 መሰረት ክለቦች ለፌዴሬሽኑ የሚጽፋቸውን ደብዳቤዎች እውነተኝነትና ሕጋዊነት ማረጋገጥ ያለበት መሆኑ ተጠቅሷል፡፡

ይሁን እንጂ ክለቡ ማስረጃ አቅርብ የተባለው አንዳንድ ዳኞች መዋለ ንዋይ በመመደብ ውጤት የሚቀይር ውሳኔ ይወስናሉ በማለት ያቀረበውን በተመለከተ ሆኖ እያለ የዳኝነት ውሳኔዎች አስመስሎ ማቅረቡ ፍፁም ተገቢነት የለውም፡፡ በተጨማሪም ክለቡ በገለፀው መሰረት ማስረጃ እስካላቀረበ ድረስ የፈፀመው የስም ማጥፋት ተግባር እንደሆነ ኮሚቴው ድምዳሜ ላይ ደርሷል፡፡

በሁለቱም የጨዋታ አመራሮች የቀረበው ሪፖርት ሲመረመር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እግር ኳስ ክለብ ስላቀረበው አቤቱታ የሚያስረዳ /የሚያረጋግጥ ምንም አይነት የቀረበ ሪፖርት የለም፡፡ አመልካች ክለቡም በወቅቱ ያቀረበው ቅሬታም ሆነ ክሰ የተመዘገበ አልተገኘም፡፡

በተጠቀሰው ቀን የተደረገውን ጨዋታ ቪዲዮ ሲታይ ክለቡ በጽሑፍ እንዳቀረበው የፌዴሬሽኑ ዳኞች ላይ እና በብሔራዊ ዳኞች ኮሚቴ ላይ ያቀረበው አስተያየት በእውነት ያልተመሰረተ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የዲስኘሊን ኮሚቴ ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተሻሽሎ በወጣው የዲስኘሊን መመሪያ አንቀጽ 72 መሰረት የሚከተለውን ውሳኔ መስጠቱን ገልጿል።

ክለቡ ለፌዴሬሽኑ የሚጽፋቸውን ደብዳቤዎች በእውነተኝነትና ሕጋዊነት ማረጋገጥ ያለበትን ግዴታውን ባለመወጣቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ማህበር ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እንዲቀጣ እና እንዲከፍል ሲወስን ክለቡ ይህ ውሳኔ በደረሰው በ7 ቀናት ውስጥ እንዲፈጽም ታዟል፡፡

You Might Also Like

ኢትዮጵያ ቡና የፋይናስ ችግር እንገጠመው ተገለፀ

“ኢትዮዽያ ቡናን ብትነኩ ከመቃብሬ ተነስቼ አጠፉቹሀለው” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ

ኢንተርናሽናል አርቢትር ማኑኤ ወ/ጻዲቅ ከአዳማ ተሰናበተ

በረከት አማረ ወደ ቀደመ ክለቡ ሊመለስ ይችላል ?

አርባምንጭ ከተማ ሴኔጋላዊ አማካይ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By Habtamu Mitku
Follow:
Writer at Hatricksport
Previous Article “ህልሜ የተሳካበት ቀን ነው” “ሻምፒዮን ስለመሆን ነው የማስበው” “የኢትዮጵያን ህዝብም ዲሲ ፓወርንም ማኩራት ነው የምፈልገው” ሎዛ አበራ ( ዲሲ ፓወር)
Next Article ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት የ20 ዓመት በታች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሴካፋ ዞን ድልድል ይፋ ሆነ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ቅዱስ ጊዮርጊስጅማ አባጅፋርየጨዋታ ዘገባቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግዜናዎች

የጨዋታ ዘገባ | የጋቶች ፓኖም ብቸኛ ግብ ለፈረሰኞቹ ሶስት ነጥብ አስገኝቷል

Habtamu Mitku By Habtamu Mitku 4 years ago
ተጠባቂው የፕርሚየር ሊጉ ጨዋታ የቀን ለውጥ ተደርጎበታል
የ2019 አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ | ኢትዮጵያ ከ ጋና በቀጥታ ውጤት /LIVESCORE/ ይከታተሉ
ቅድመ ጨዋታ ዕይታ| ወልቂጤ ከ ባህርዳር ከተማ
አህመድ ሁሴን ለአንድ ወር ከሜዳ ይርቃል
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?