የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ተወዳዳሪ የሆኑት ጅማ አባ ጅፋሮች መውረዳቸውን ካረጋገጡ ሶስት ክለቦች አንደኛው ናቸው ።
የጅማ አባ ጅፋር ተጫዋቾች ላለፉት ሁለት ወራት ደሞዝ አለመከፈላችውን ተከትሎ ልምምድ ካቆሞ ሁለት ቀናት ተቆጥረዋል ።
በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር ተከትሎ የጅማ አባ ጅፋር እግር ኳስ ክለብ ያለፉትን ሁለት ቀናት መደበኛ ልምምዳቸውን አለመስራታቸው ታውቋል ። ተጨዋቾቹ ለክለቡ አመራሮች ደሞዝ እንዲከፈላቸው በተደጋጋሚ ቢጠይቁም ክለቡ መክፈል እንደማይችል ተነግሯቸዋል ።
በ26ኛ ሳምንት የመርሀ ግብሩ የመጨረሻ ጨዋታ ሀዲያ ሆሳዕናን እሚገጥሙት ጅማ አባጅፋሮች የነገውን ጨዋታ የማካሄዳቸው ነገር ጥያቄ ውስጥ ወድቋል።
አስተያየት ይስጡ