በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ እየተመሩ ረፋድ ላይ አንጋፋውን የመሀል ሜዳ ተጫዋች መስዑድ መሀመድን ከሰበታ ከተማ ያስፈረሙት ጅማዎች አሁን ደግሞ ተጨማሪ አራት ተጫዋቾችን ማስፈረማቸዉ ታዉቋል።
በአዳማ ከተማ ቤት ረዘም ላለ አመታት የተጫወተው የመስመር ተከላካዩ ሱለይማን መሀመድ በዛሬዉ ዕለት ለጅማ አባጅፋር ለመጫወት ፊርማዉን ያኖረ ሁለተኛዉ ተጫዋች ሆኖአል። ከዚህ በፊት በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤት መጫወት የቻለዉ ሱለይማን በአባጅፋር ቤት ከቀድሞ አሰልጣኙ አሸናፊ በቀለ ጋር የሚገናኝም ይሆናል።
ሌላኛዉ ክለቡን የተቀላቀለዉ ተጫዋች ደግሞ ወጣቱ አማካይ ሚካኤል ሀሲሳ መሆኑ ታዉቋል። በሲዳማ ቡና እግርኳስ ቡድን ዉስጥ ከታዳጊነት አንስቶ እስከ ዋናዉ ቡድን ሲጫዎት የምናዉቀዉ አማካዩ አሁን ደግሞ ወደ ጅማ አባጅፋር ማምራቱ ተረጋግጧል።
በአራተኝነት ወደ ክለቡ ያመራው ደግሞ የመስመር አጥቂዉ እዮብ አለማየሁ መሆኑ ታዉቋል። አጥቂዉ ረዘም ላሉ አመታት ከተጫወተበት ወላይታ ዲቻ በመልቀቅ በዛሬዉ ዕለት ጅማ አባጅፋርን መቀላቀሉ ተሰምቷል።
- ማሰታውቂያ -
ሌላኛዉ በዛሬዉ ዕለት አምስተኛ ፈራሚ ሁኖ ጅማ አባጅፋርን የተቀላቀለዉ ደግሞ ዱላ ሙላቱ መሆኑ ታዉቋል። የመስመር ተጫዋቹ የዉድድር አመቱን ከሀድያ ሆሳዕና ጋር ካሳለፈ በኋላ ለሁለት ዓመታት በሚቆይ ዉል ጅማ አባጅፋርን መቀላቀሉ ተገልጿል። ተጫዋቹ ከዚህ ቀደም በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ስር በአዳማ ከተማ እና ሀድያ ሆሳዕና መሰልጠኑ ይታወሳል።