ከአሰልጣኝ ፀጋየ ኪዳነማርያም ጋር ከተለያዩ በኋላ አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለን በዋና አሰልጣኝነት የቀጠሩት ጅማ አባጅፋሮች አሁን ደግሞ ወደ ዝዉዉሩ በመግባት የቀድሞ ተጫዋቻቸዉን መስዑድ መሀመድ ማስፈረማቸዉ ታዉቋል።
የቀድሞው ኢትዮጵያ ቡና የመሐል ተጫዋች እና ክለቡን በ2011 ከለቀቀ በኃላ ወደ ጅማ ያመራዉ መስዑድ አንድ አመት ቆይታ በኋላ ወደ ሰበታ ከተማ አምርቶ ሁለት የውድድር ዓመታትን በሰበታ ከተማ ቤት ማሳለፉ ይታወቃል። አሁን ደግሞ ሁለት አመታትን ካሳለፈበት ሰበታ ቤት በመልቀቅ የቀድሞ ክለቡን ጅማ አባጅፋርን መቀላቀሉ ተረጋግጧል።


