By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “ኢትዮጵያ ቡናን ለሚያህል ታላቅ ቡድን በእዚህ ፍጥነት እጫወታለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር” ዊሊያም ሰለሞን /ኢትዮጵያ ቡና/
Share
Notification Show More
Latest News
በጨምበላላ ዋዜማ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጣፋጭ ድል ቀምሷል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የጨዋታ ዘገባ
ዩጋንዳዊው የሲዳማ ቡና ግብ ጠባቂ በዛሬው ጨዋታ አይሰለፍም
ሲዳማ ቡና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች
የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ አመራሮች ከሀላፊነት ለመነሳት ፍቃደኛ ሆኑ
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
የሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ ታገደ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ሲዳማ ቡና
መቐለ 70 እንደርታ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች መቐለ 70 እንደርታ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

“ኢትዮጵያ ቡናን ለሚያህል ታላቅ ቡድን በእዚህ ፍጥነት እጫወታለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር” ዊሊያም ሰለሞን /ኢትዮጵያ ቡና/

መሸሻ ወልዴ
መሸሻ ወልዴ 5 years ago
Share
SHARE

 

በሐረር ከተማ ተወልዶ ያደገው ዊሊያም ሰለሞን በታዳጊነት ዕድሜው ለኢትዮጵያ ወጣቶች አካዳሚ ቡድን ለመሰልጠንና ለመጫወት ወደ አዲስ አበባ ከመጣ በኋላ የትውልድ ሀገሩ ላይ ስለ ኢትዮጵያ ቡና ከሚሰማው ነገር በመነሳት የክለቡ ደጋፊ ለመሆን እንደቻለ እና ዛሬ ላይ ደግሞ ፈፅሞ ባልጠበቀው መልኩ የእዚሁ ትልቅ ቡድን ተጨዋች ሆኖ የክለቡን መለያ በማጥለቅ ሊጫወት በመቻሉ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማው ለሀትሪክ ስፖርት ድረ ገፅ አስተያዩቱን ሰጥቷል።

ኢትዮጵያ ቡናን በዝውውር መስኮቱ ከመከላከያ ክለብ በመምጣት የተቀላቀለው እና በቤትኪንግ የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታ ላይም ተቀይሮም ሆነ በቋሚ ተሰላፊነት በመግባት የተጫወተው እና ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴንም ያሳየው ዊሊያም 58 ኪሎ ግራም የሚመዝን ሲሆን 1ሜትር ከ61 ሜትርም ይረዝማል። ይህን ተጨዋች ከኳስ ጅማሬው አንስቶ አሁን ኢትዮጵያ ቡናን እስከተቀላቀለበት እና ለቡድኑም ተሰልፎ ለመጫወት እስከቻለበት ጊዜ ድረስ ባሉት ጉዳዮች ዙሪያ ጋዜጠኛ መሸሻ ወልዴ አናግሮት የሰጠው ምላሽ የሚከተለውን ይመስላል።

ስለ ኳስ ጅማሬው

- ማሰታውቂያ -

“የኳስ ጅማሬዬ ተወልጄ ባደግኩበት ሐረር ከተማ ፖሊስ ሜዳ ላይ ነው፤ እዛም ነው ከህፃንነት ዕድሜዬ አንስቶ የምወደውን ኳስ ለመጫወት የቻልኩት”።

ኳስን መጫወት ሲጀምር ቤተሰብ ጋር ስለነበረው አመለካከት

“እነሱ ኳስ መጫወቴን ይደግፉት ነበር። ከዛ በተጨማሪ ትምህርቴንም እንድማርም ጭምር ያበረታቱኝ ነበርና የእነሱ ድጋፍና እገዛ ከፍ ያለ ነበር”።

ከዊልያም ውጪ በሌላም ስም ስለመጠራቱ

“አዎን። ሐረር ላይ አበጋዝ ብለው የሚጠሩኝ አሉ።”

በታዳጊነት ዕድሜው ኳስን መጫወት ሲጀምር አድንቆት ስላደገው ተጨዋች

“ይሄ ተጨዋች አቤል እንዳለ ይባላል። ለደደቢት ተጫውቶ ካሳለፈ በኋላ በአሁን ሰዓት ላይ ደግሞ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በመጫወት ላይ ይገኛል። እሱን ነው የኳስ ተምሳሌቴ አድርጌ ያደግኩት። አቤል በሐረር ከተማ ውስጥም የሰፈሬ ልጅ ነው። በአካባቢያችን በኳሱም አሉ ከሚባሉት ተጨዋቾች መካከልም አንዱ ነው።

የእግር ኳስን ተጫውቶ ስለመጣበት መንገድ

“መጀመሪያ ተወልጄ ባደግኩበት ሐረር ውስጥ ነው በታዳጊነት ዕድሜዬ በ2006 እና 2007 ላይ የተጫወትኩት። ከዛም ወደ ኢትዮጵያ ወጣቶች አካዳሚ ገባውና ለሁለት ዓመታት ቆየው። በመቀጠል ደግሞ የመከላከያ u-20 ቡድንን በ2011 ለመቀላቀል ቻልኩና ከሐዋሳ ከተማ ጋር ባደረግነው ጨዋታ ጥሩ መንቀሳቀሴን ተከትሎ በአንድ ጨዋታ በአሰልጣኝ ስዩም ከበደ አማካኝነት ወደ ዋናው ቡድን የማደግ ዕድሉን አገኘውና ቡድኑ በወረደበት ዓመት ላይ የመሰለፍ እድሉን አላገኘውም ነበር። አምና በነበረን የከፍተኛ ሊግ ቆይታ ደግሞ በአሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው አማካኝነት ለመከላከያ ዋናው ቡድን በበቂ ሁኔታ የመሰለፍ እድሉን አግኝቼ ከተጫወትኩ በኋላ ዘንድሮ ኢትዮጵያ ቡናን ተቀላቀልኩ”።

ወደ ኢትዮጵያ ቡና እንዴት እንዳመራ

“ኢትዮጵያ ቡናዎች እኔን ወደ ክለባቸው እንድመጣ ማናገርና ፍላጎታቸውን ማሳየት የጀመሩት ባሳለፍነው ዓመት ግማሽ ላይ ነበር። ያኔ እኔ ያደግኩበትን ክለብ መጥቀምና ችሎታዬን ማሳደግ እፈልግ ስለነበር እንደዚሁም ደግሞ ውልም ስለነበረብኝ ይሄ አልተሳካም። በኋላ ላይ ኮቪድ ገብቶም ስለነበር በድጋሚ በክረምቱ ወራት ላይ አናገሩኝና የእኔ ዝውውር በስተመጨረሻም ተሳካ”።

ወደ ኢትዮጵያ ቡና የተዛወርከው እና ከመከላከያ ጋር የተለያየከው በአሰልጣኝ ዩሃንስ ሳህሌ ስላልተፈለግክ ነው?

“እውነታውማ ይሄ አይደለም። አሰልጣኝ ዩሃንስማ እኔን በጣም ይፈልገኛል። ከዛ ውጪም ወደ ቡድኑ ሲመጣ እኔን ጨምሮ ወደ ዋናው ቡድን አምና አድገን በነበርነው አራት ልጆች ላይ ሌሎችንም ጨምሮ ቡድኑን መስራት እንደሚፈልግም ነበር የነገረን። እኔን በተለይ በጣም ያበረታታኝና /አፕርሸትም/ ያደርገኝ ነበር። በጋራ ጥሩ ነገር እንሰራለንም ብሎኝ እና ደሞዜ ተጨምሮልኝ ከቡድኑ ጋር እንድቀጥልም ይፈልግ ነበር። ከእሱ ውጪ ከረዳቱ አሰልጣኝ ዮርዳኖስ አባይ ጋርም አውርተን እሱም ስለእኔ ጥሩ ነገር ነበረው። ይሄ ሆኖ ሳለ ግን የእኔን እድገት በማይፈልግ እና ቡድኑ ውስጥ ባለ አንድ ሰው ምክንያት ነው መናገር በማልፈልጋቸው ብዙ ጉዳዮች ከክለቡ ጋር ለመለያየትና ቡናንም ለመቀላቀል የቻልኩት”።

ወደ ኢትዮጵያ ቡና ሲገባ እና መለያውን አድርጎ ሲጫወት ስለተሰማው ስሜት

“ለቡድኑ መጫወት እፈልግ ነበር። ይህ እልሜ ከበፊት ጀምሮም አብሮኝ የነበረም ስለሆነ ወደ ቡድኑ ስገባና ማሊያውንም አጥልቄ ስጫወት የተለየ ደስታ ነበር የተሰማኝ”።

ወደ ኢትዮጵያ ቡና በፍጥነት እንዲህ እገባለው ብለህ ጠብቀህ ነበር?

“በፍፁም። ኢትዮጵያ ቡናን ለሚያህል ታላቅ ቡድን በእዚህ ፍጥነት ገብቼ እጫወታለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር። ይሄ እድለኛነቴን ነው የሚያሳየው”።

የኢትዮጵያ ቡና ካምፕን ስትቀላቀል ቡድኑን በአንዴ ተላመድክ? አቀባበላቸውስ ምን ይመስል ነበር?

“ወደ ቡድኑ ስመጣ ምርጥ አቀባበል ነበር ያደረጉልኝ። በተለይ ደግሞ አቡበከር ናስርና እያሱ ታምሩ ክለቡን ቶሎ እንድላመድ ያደረጉት ጥረትም ደስ የሚልም ነበርና በአጠቃላይ የቡናን ተጨዋቾች አመሰግናቸዋለሁ”።

በኢትዮጵያ ቡና ቆይታህ ምን ነገሮችን ታልማለህ? የጨዋታ ጅማሬህስ…

“ወደ ቡድኑ በገባሁበት አጭር ጊዜ ውስጥ ከወዲሁ አበረታች የሚባል እንቅስቃሴን ለማሳየት ብችልም ገና ብዙ የሚጠበቅብኝ ተጨዋች ነኝ። በቡና ቆይታዬም ቡድኑን ከእዚህ በላይ አገልግዬና ሻምፒዮና ሆኜም ታሪክ መስራትም እፈልጋለሁ”።

ስለ አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ

“እሱን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደተመለከትኩት ከምንም ነገር በላይ አባት ጓደኛ እና ለሁሉም ተጨዋች እኩል አይነት አመለካከት ያለው እና ያመነበትን ነገር በማሰብ የሚሰራ ምርጥ ባለሙያ ነው። ከዛ በተጨማሪ እንደ ሌሎች አሰልጣኞች የመኩራራት ባህሪም አይታይበትምና ይሄን በጣም ወድጄለታው”።

ስለ ኢትዮጵያ ቡና ወቅታዊ አቋም እና ቡድኑ የት ድረስ እንደሚጓዝ

“ጥሩ ላይ ነው ያለነው። ተነሳሽነታችን እና ፍላጎታችንም በጣም የሚገርም ነው። ከሌሎች ቡድኖች አንፃርም ብዙዎቹ የአየር ላይ ኳስን ስለሚጠቀሙ በተጠና እና በተቀናጀ መልኩ የሚጫወት ቡድንን ከእኛ በላይ ያየሁበት ክለብ ስለሌለም የዘንድሮ የሊግ ዋንጫውን ለማንሳት ይከብደናል ብዬ አላስብምና እስከ ፍፃሜው ድረስ ነው የምንጓዘው”።

የእግር ኳስ እድገትህ ፈጣን ነው ማለት እንችላለን?

“አዎን። ከሐረር አንስቶ የእኔ እዚህ ደረጃ ላይ በፍጥነት መድረስ የሚታሰብ አይደለም። ሐረር በነበርኩበት ሰዓት ክለብ ያላገኙ ልጆች ብዙ ናቸው እኔ ግን በእዚህ የወጣትነት እድሜዬ ያውም ቡናን ወደሚያክል ክለብ መግባቴን ሳስብ ፈጣሪዬን አመሰግነዋለሁ”።

በመጨረሻ

“የእግር ኳስ ተጨዋችነት ጅማሪዬ እና ጉዞዮ በሀገር ውስጥ ተጨዋችነት ብቻ ተገድቦ እንዲቆም አልፈልግም። ወደ አውሮፓ ወጥቶ መጫወትን እፈልጋለሁ። ከዛ በፊትም በአሰልጣኝ ካሳዬ አራጌ ከሚመራው ቡድን ቡናም ጋር ዋንጫን ማንሳት እና ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንም መጫወትን እፈልጋለሁ እና ለዛ ጠንክሬ እሰራለሁ። ከዛ ውጪ መናገር የምፈልገው ለእዚህ ደረጃ እንድበቃ ያደረጉኝን ቤተሰቦቼን የልጅነት አሰልጣኜን እስክንድርን እና እስከዛሬ ብዙ ነገርን ያደረገልኝን አቤል እንዳለን በፈጣሪ ስም ከልብ አመሰግናቸዋለሁ”።

You Might Also Like

በጨምበላላ ዋዜማ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጣፋጭ ድል ቀምሷል

ዩጋንዳዊው የሲዳማ ቡና ግብ ጠባቂ በዛሬው ጨዋታ አይሰለፍም

የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ አመራሮች ከሀላፊነት ለመነሳት ፍቃደኛ ሆኑ

የሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ ታገደ

መቐለ 70 እንደርታ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By መሸሻ ወልዴ
Follow:
Editor at Hatricksport website
Previous Article “ከእኔ የማይጠበቅ ስህተት ሰርቼ ቡድናችን አሸናፊ እንዳይሆን ስላደረግኩ ቡድኔን፣ አሰልጣኜን፣ ተጨዋቾቻችንን እና ደጋፊዎቻችንን ይቅርታ እጠይቃለሁ” ምንይሉ ወንድሙ /ባህር ዳር ከተማ/
Next Article የጨዋታ ዘገባ | ሲዳማ ቡና የአመቱን የመጀመሪያ ድል አሳካ

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ሀትሪክ ስፖርት አትሌቲክስታላቁ ሩጫቨረችዋል ታላቁ ሩጫ

የሁለተኛው ዙር የ5ኪሜ ቨርቹዋል ሩጫ ምዝገባ በዛሬው እለት በሚሊኒየም ፓርክ ችግኝ በመትከል በይፋ ተከፍቷል

kidus Yoftahe By kidus Yoftahe 6 years ago
ሃዋሳ ከተማ፣ድሬደዋ ከተማ፣ቅዱስ ጊዮርጊስ እና መቐለ 70 እንደርታ ቅጣት ተላልፎባቸዋል
የዋሊያዎቹ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች 180 ሺህ ዶላር ተሸጡ
ሰበር ዜና:- ሊግ ካምፓኒው ዛሬ ባደረገው ስብሰባ አዳዲስ ውሳኔዎችን አስተላለፈ…..
ETHIOPIAN PREMIER LEAGUE DEBUTS TODAY
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
 

Loading Comments...
 

    Welcome Back!

    Sign in to your account

    Lost your password?