By using this site, you agree to the Privacy Policy and Terms of Use.
Accept
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Reading: “ለቅዱስ ጊዮርጊስ ባይመጥንም በኮንፌዴሬሽን ካፕ ለመሳተፍ ብለን ጠንክረን እየሰራን ነው” ምንተስኖት አዳነ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/
Share
Notification Show More
Latest News
በጨምበላላ ዋዜማ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጣፋጭ ድል ቀምሷል
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች የጨዋታ ዘገባ
ዩጋንዳዊው የሲዳማ ቡና ግብ ጠባቂ በዛሬው ጨዋታ አይሰለፍም
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ሲዳማ ቡና
የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ አመራሮች ከሀላፊነት ለመነሳት ፍቃደኛ ሆኑ
ዜናዎች ቅዱስ ጊዮርጊስ
የሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ ታገደ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዜናዎች ሲዳማ ቡና
መቐለ 70 እንደርታ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ
የዝውውር ዜናዎች ዜናዎች መቐለ 70 እንደርታ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ
Aa
ሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያሀትሪክ ስፖርት ኢትዮጵያ
Aa
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
  • መነሻ ገፅ
  • ዜናዎች
  • ፕሪሚየር ሊግ
    • ባህርዳር ከተማ
    • ወላይታ ዲቻ
    • ድሬዳዋ ከተማ
    • ፋሲል ከነማ
    • ሲዳማ ቡና
    • አዳማ ከተማ
    • ሀዋሳ ከተማ
    • ቅዱስ ጊዮርጊስ
    • ኢትዮጵያ ቡና
    • ጅማ አባጅፋር
    • ወልቂጤ ከተማ
    • ሰበታ ከተማ
    • ሀዲያ ሆሳዕና
  • ዋልያዎቹ
  • ውድድሮች
  • English Article
  • French Articles
  • ስለ እኛ
Have an existing account? Sign In
Follow US
  • Advertise
© 2023 Hatrick Spoert. Design by Tech-ethiopia.com All Rights Reserved.
ዜናዎችቅዱስ ጊዮርጊስቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

“ለቅዱስ ጊዮርጊስ ባይመጥንም በኮንፌዴሬሽን ካፕ ለመሳተፍ ብለን ጠንክረን እየሰራን ነው” ምንተስኖት አዳነ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/

ዮሴፍ ከፈለኝ
ዮሴፍ ከፈለኝ 5 years ago
Share
SHARE

ሀትሪክ፡- ቅዱስ ጊዮርጊስ በ34 ነጥብ 3ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል በኮንፌዴሬሽን ካፕ ለመሳተፍ ያላችሁ እድል ለመጠቀም ምን ያህል እየተዘጋጃችሁ ነው?

ምንተስኖት፡- እውነት ለመናገር 2ኛ ሆኖ በኮንፌዴሬሽን ካፕ መሳተፍ ለጊዮርጊስ የሚመጥን አይደለም፡፡ አሁን ግን ያለን እድል ይሄ ቦታ ብቻ በመሆኑ በኮንፌዴሬሽን ካፕ ለመሳተፍ ብለን ጠንክረን እየሰራን ነው በቀሪ 3 ጨዋታዎች 9 ነጥብ የግድ ያስፈልገናል የኢትዮጵያ ቡና ነጥብ መጣልን ጠብቀን እድሉን ለመጠቀም 3ቱን ጨዋታ ለማሸነፍ የምንችለውን እናደርጋለን ብለን እናስባለን፡፡

ሀትሪክ፡- ከሲዳማ ቡና ጋር በነበራችሁ ጨዋታ ላይ ደካማ አቋም ነው ያሳያችሁት…ምክንያቱ ምን ይሆን?

ምንተስኖት፡- እውነት ነው ጥሩ አልነበርንም የግብ ሙከራም አሳዳረግንም አቋማችንም ልክ አይደለም ጥሩ የውድድር አመት ነው ያሳለፍነው ማለት አልችልም ብዙ ጨዋታ ተሸንፈናል አቻም ወጥተናል ይሄ የቅዱስ ጊዮርጊስ አቋምም አልነበረም፡፡ ከሲዳማ ቡና ጋር ካደረግነው ጨዋታ አስቀድሞ ከባህርዳር ከተማ ጋር በከፍተኛ ተነሳሽነት ስንጫወት ነበር የዝናም ጨዋታ በመሆኑ ከፍተኛ ጉልበትን አውጥተን ነበርና ድካም ተሰምቶን እንደነበር ያስታውቃል እንደ ብቸኛ ምክንያት ባይሆንም ድካሙ አስተዋፅኦ አድርጓል ብዬ አምናለው በሜዳ ላይ የነበረው እንቅስቃሴም ጥሩ አልነበረምና ሲዳማ ቡና በተቃራኒው የግብ እድሎችን ፈጥሮ ሁለት ግቦችንም አስቆጥሮ አሸንፎናል፡፡

- ማሰታውቂያ -

ሀትሪክ፡- በዚህ አያያዝ 2014 ለቅዱስ ጊዮርጊስ አያሰጋም?

ምንተስኖት፡- ትልቅ የቤት ሥራ ይጠብቀናል አሁን ያለው እውነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻምፒዮን ሲሆን እንደነበረው ጊዜ አይደለም… ጠንካራ ቡድኖች ተፈጥረዋል ሁሉም ቡድኖች ዋንጫ መውሰድ ይቻላል የሚል እምነት ውስጥ ገብተዋልና ፉክክሩን ጠንካራ አድርጎታል፡፡ አሁንም ቢሆን ጥሩ የተጨዋቾች ስብስብ አለን ጥራት ያለው እኛ ጋር ነው እንደቡድን ለመጫወት የተሻለ ስራ ይጠበቅብናል እንጂ ክፍተት ባለው ቦታ ላይ ማስተካከያ ከተደረገበት ጥሩ ቡድን እንደምንሆን አልጠራጠርም የሚታወቀውን ኃያልነት ለመመለስ እንቸገራለን ብዬም አልሰጋም፡፡

ሀትሪክ፡- ከውጪ ሀገር አሰልጣኝ ይልቅ ኢትዮጵያዊ አሰልጣኝ ይሻላል የሚሉ ወገኖች አሉ ትስማማለህ…?

ምንተስኖት፡-የውጪ አሰልጣኝ ችግር ነው ብዬ አላምንም በክለብ ደረጃ የተጫወትኩት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ብቻ ነው፤ በጊዮርጊስ ማሊያ የሰለጠንኩት በውጪ አሰልጣኝ ብቻ ነው… በውጪ አሰልጣኞች ዋንጫ አምጥተንም እናውቃለን ራሣቸውን በሚገባ ያሳዩ የውጪ አገር አሰልጣኞች አሉኮ… ችግሩ የእነሱ ነው ብዬ አላምንም ከወቅታዊ ደካማ አቋማችን ጋር ተያይዞ እንጂ በነጮቹ አሰልጣኞች ውጤት አምጥተናል፡፡ በውጪ አሰልጣኞችም ዋንጫ አይወሰድም ብዬም አላምንም… የትኛው የተሻለ ይጠቅማል የሚለውን የሚያውቀው ደግሞ ክለቡ ይመስለኛል፡፡

ሀትሪክ፡- ቀጣይ ጨዋታ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ነው ሀዲያ ሆሳዕና በወቅታዊ አቋሙ ደካማ ነው እየተባለ ነውና ከጨዋታው…3 ነጥብ አይገኝም?

ምንተስኖት፡- ጨዋታው ይቀለናል ብዬ አልጠብቅም ኢትዮጵያ ውስጥ የተጨዋች ልዩነት አለ ብዬ አላምንም ሁሉም ተጨዋች አንድ ነው ሠፈር ውስጥ ያለው፣ ታዳጊ ነው የሚባለው ሲኒየር የሚባለው ጭምር በሙሉ ልዩነቱ ልምዱ ብቻ ይመስለኛል ኢትዮጵያ ውስጥ ከሳላሀዲን ሰይድ ውጪ ሁሉም ተጨዋች እንደ ቻይና ህዝብ ተመሳሳይ ነው /ሳቅ/ እናም ልዩነት አለው ብዬ አላምንም ታዳጊዎች ቢሆኑም በትልቅ ተነሳሽነት ነው የሚገጥሙን… ራሣቸውን ለማሳየት ስለሚጥሩም ጨዋታው ይከብዳል ብዬ አምናለሁ፡፡ ወጣቶቹ ጉልበት አላቸው ከሰበታ ከተማ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ጥሩ ተፎካክረው ባለቀ ሰዓት በተቆጠረ ግብ ነውና የተሸነፉት ቀላል ተጋጣሚ ናቸው ብለን አናስብም ነገር ግን 9 ነጥብ ስለሚያስፈልገን ይህን ጨዋታ ጨምሮ ሌሎቹን ሁለቱን ጨዋታዎች ማሸነፋችን የግድ ነው፡፡

You Might Also Like

በጨምበላላ ዋዜማ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ጣፋጭ ድል ቀምሷል

ዩጋንዳዊው የሲዳማ ቡና ግብ ጠባቂ በዛሬው ጨዋታ አይሰለፍም

የቅዱስ ጊዮርጊስ የቦርድ አመራሮች ከሀላፊነት ለመነሳት ፍቃደኛ ሆኑ

የሲዳማ ቡናው ግብ ጠባቂ ታገደ

መቐለ 70 እንደርታ ናይጄሪያዊ አጥቂ አስፈረመ

Share this Article
Facebook Twitter Email Print
By ዮሴፍ ከፈለኝ
Follow:
Editor at Hatricksport
Previous Article Abubeker Nassir breaks Getaneh Kebede‘s 4-year-old goal scoring record.
Next Article “ለ2ኛነት ቦታ ተስፋ ባንቆርጥም ከባድ ፍልሚያ ግን ይጠብቀናል ብዬ እሰጋለሁ” /ሚካኤል ጆርጅ/ሀድያ ሆሳዕና/

Follow US

Find US on Social Medias
127k Like
2.9k Follow
1.6k Follow
19.7k Follow

Weekly Newsletter

Subscribe to our newsletter to get our newest articles instantly!

ተነባቢ ዜናዎች
ዜናዎች

የዋልያዎቹ የቀድሞው አሰልጣኝ በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ሀላፊ ሊሆኑ ነው

kidus Yoftahe By kidus Yoftahe 5 years ago
ሀትሪክ አበይት ጉዳዮች| የ10ኛ ሳምንት ዋና ዋና ጉዳዮች
“በኮንፌዴሬሽን ካፑ ምድብ ድልድል ውስጥ መግባትናየሊጉን ዋንጫ ለማንሳት አቅደናል”ወንድሜነህ ደረጄ /ኢትዮጵያ ቡና/
ፋሲል ተከላካይ አስፈርሟል
ከወርቅም በላይ አልማዝ የሆነችው አልማዝ አያና የመጀመሪያውን ወርቅ ለሀገርዋ አበረከተች
- Advertisement -
Ad imageAd image
Global Coronavirus Cases

Confirmed

0

Death

0

More Information:Covid-19 Statistics
about us

Phone: 0993808668 Email: [email protected] .

Find Us on Socials

© Hatrick Sport 2023 All Rights Reserved.

Removed from reading list

Undo
Welcome Back!

Sign in to your account

Lost your password?