*..ወጣቱ ኮከብም የስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈራርሟል…
ጎፈሬ የትጥቅ አምራችና ሀዋሳ ከተማ የእግር ኳስ ቡድን የ3 አመት የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራረሙ።
የጎፈሬ ትጥቅ አምራች ኩባንያ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሳሙኤል መኮንን “ከ17 አመት ጀምሮ እስከ ዋናው ቡድን
የልምምድ ፣የጉዞ፣በሜዳና ከሜዳ ውጪ ምግብ መመገቢያ ማሊያና ቱታዎችን እናቀርባለን ውሉ አትሌቲክስ ቡድኑንም የሚመለከት ሲሆን በሶስት አመት ውል መሠረት እስከ 2 ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ ዋጋ ያለው ትጥቅ ለክለቡ እናቀርባለን ድርጅታችን በውሉ መሠረት ወደ 10 ሺህ ማሊያ ለደጋፊ ያቀርባል በስምምነቱም ደስተኛ ን” ሲሉ ተናግረዋል።
የሀዋሳ ስፖርት ክለብ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኡቴሳ ኡጋሞ በበኩላቸው “ክለባችን ከታዳጊ ማለትም ከ13 አመት እስከ ዋናው ቡድን በስሩ አቅፏል ለነኚህ ቡድኖች ደግሞ ትጥቅ ከውጭ ስናመጣ ቆይተናል አሁን ግን ጨገር በቀል ከሆነው ጎፈሬ ጋር በመነጋገር የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራርመናል በቀጣዮቹ ሶስት አመት በጋራ አብረን እንደምንሰራ ተስፋ እናደርጋለን” በማለት ተናግረዋል።
በተመሳሳይ ጎፈሬ ትጥቅ አምራች ኩባንያም ከአመቱ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ወጣት ተጨዋች ከሆነው ወንድማገኝ ሃይሉ ጋርም የስፖንሰርሺፕ ስምምነት ተፈራርሟል።

ሁለቱ ወገኖች ለቀጣዮቹ ሁለት አመታት አብረው ለመስራት የተስማሙ ሲሆን ኳስ ተጨዋቾች አምባሳደር መሆን እንደሚችሉ ማሳየትና በይፋ ያልተደረገ ክፍያ በየሶስት ወሩ የሚከፈለው ይሆናል ተብሏል። በውሉ ላይ የባለሙያ ድጋፍና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ተካተውበታል ተጨዋቹም “በስምምነቱ ተደስቻለሁ እንደ ወጣት የተቻለኝን ለማድረግ እጥራለሁ”ብሏል።
ሀዋሳ ከተማ ለወንድማገኝ ከመስከረም ወር ጀምሮ ይከፈለው ከነበረው ደመወዝ አራት እጥፍ እንዲከፈለው መወሰኑም ታውቋል።
አስተያየት ይስጡ