አሰልጣኝ ዘርዐይ ሙሉን ከቀጠሩ በኋላ ወደ ዝዉዉር ገበያዉ በመግባት ተጫዋችን በማስፈረም እና የነባሮቹን ዉል በማደስ ላይ የሚገኙት ሀዋሳ ከተማዎች አሁን ደግሞ አማካዩን በቃሉ ገነነን ከአዳማ ከተማ ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።
በ2013 የውድድር አመት ምንም እንኳን ክለቡ አዳማ ከተማ ዉጤታማ ባይሆንም ተጫዋቹ በግሉ ጥሩ የሚባል እንቅስቃሴን በማድረግ አጠናቋል። በተለይ ዳግም ወደ ሊጉ ለመመለስ በተካሄደው የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዉድድር ላይ ክለቡ አዳማ የአንደኝነት ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ ትልቅ ድርሻ የነበረዉ ተጫዋቹ አሁን ደግሞ የቀድሞዉን አሰልጣኝ ዘርዓይ ሙሉ በመከተል ፊርማዉን ለሀይቆቹ ማኖሩ እርግጥ ሆኖአል።
እስከ አሁን ድረስ ሁለት ተጫዋቾችን ያስፈረሙት ሀዋሳ ከተማዎች በቀጣይም አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ እንደሚቀላቅሉ ይጠበቃል።