አሰልጣኝ ሙሉጌታ ምህረትን በዋና አሰልጣኝነት ከቀጠሩ በኋላ ወደ ዝዉዉር የገቡት ሀድያ ሆሳዕናዎች የሁለት ተጫዋቾችን ዝዉዉር ማጠናቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።
ዉድድር አመቱን በአሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ እየተመሩ ጥሩ አጀማመርን ማድረግ ቢችሉም የኋላ ኋላ ከተጫዋቾቻቸዉ ጋር በገቡት አለመግባባት ምክንያት እንደ አጀማመራቸዉ መሆን ሳይችሉ ቀርተዉ ሊጉን በ4ኛ ደረጃ ማጠናቀቃቸው ይታወቃል።
አሁን ደግሞ ለቀጣዩ የዉድድር አመት ተጠናክረዉ ለመቅረብ ይረዳቸዉ ዘንድ የአማካይ ስፍራ ተጫዋቾቹን ፍቅረየሱስ ተ/ብርሀንን ከኢትዮጵያ ቡና እና ፍሬዘር ካሳን ከድሬዳዋ ከነማ ማስፈረማቸዉ ተረጋግጧል።

- ማሰታውቂያ -
ሀዋሳ ከነማን ከለቀቀ በኋላ በቡናማዎቹ ቤት ያሳለፈው ፍቅረየሱስ በ2014 የዉድድር አመት በሀድያ መለያ የምንመለከተው ተጫዋች ሆኖአል። ሌላኛዉ ክለቡን የተቀላቀለዉ ደግሞ የመስመር ተከላካይ ተጫዋች የሆነዉ ፍሬዘር ሲሆን ዘንድሮ በሊጉ ምንም እንኳን ክለቡ ድሬዳዋ ይህ ነዉ የሚባል የተለየ ዉጤታማነት ባይታይበትም በግሉ ተጫዋቹ ጥሩ አመት ማሳለፉ ይታወሳል።


