በ2014 ዓ.ም የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዉድድር ላይ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነዉ ለመቅረብ ይረዳቸዉ ዘንድ በክረምቱ የዝዉዉር መስኮት የተለያዩ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ስብስባቸዉ ሲቀላቅሉ የቆዩት ሀድያ ሆሳዕናዎች አሁን ደግሞ የመስመር ተጫዋቹን አስቻለው ግርማ ማስፈረማቸዉ ተሰምቷል።
ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ቡና ፣ ሀዋሳ ከተማ ፣ ጅማ አባጅፋር ፣ ሰበታ ከተማ አና ድሬዳዋ ተጫዉቶ ማሳለፍ የቻለዉ አጥቂዉ አስቻለዉ ግርማ የ2014ን የዉድድር አመት በሀድያ ሆሳዕና መለያ የምንመለከተው ይሆናል።
አስተያየት ይስጡ