መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና የሀድያ ሆሳዕና ክለብ ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር በተያያዘ በድጋሚ ችግር ውስጥ ገብቷል
ሀዲያ ሆሳዕናቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግዜናዎች

የሀድያ ሆሳዕና ክለብ ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር በተያያዘ በድጋሚ ችግር ውስጥ ገብቷል

አጋራ
አጋራ

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ የሆነው የሀድያ ሆሳዕና ክለብ በ2013 የውድድር አመት ከተጫዋቾች ክፍያ ጋር በተያያዘ ብዙ ውዝግቦችን ማስተናገዱ ይታወሳል ። ከአምናው ስህተቱ የተማረ የማይመስለው ክለቡ የውድድር አመቱ ገና ከመጀመሩ ከተጫዋቾቹ ጋር አለመግባባት ውስጥ ገብቷል ።

በሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታ ከፋሲል ከተማ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ ሰአታት በቀሩበት ጊዜ 12 ተጫዋቾች ከክለቡ ጋር የተስማማነውን የፊርማ ገንዘብ ሊያስገቡልን ፈቃደኛ አልሆኑም በማለት ጨዋታውን አናደርግም አሉ ። ነገር ግን በዋና አሰልጣኙ ሙሉጌታ ምህረት ተማፅኖ ጨዋታውን አድርገዉ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል ።

ከዚህ ጨዋታ በኋላ እነዚህ 12 ተጨዋቾች ከክለቡ ጋር ልምምድ መስራት ያቆሙ ሲሆን የክለቡ አመራሮች ክፍያውን የማይፈፅሙላቸው ከሆነ በነገው ዕለት ከባህር ዳር ከተማ ጋር ያላቸውን ጨዋታ እንደማያደርጉ ተናግረዋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በዝናባማው ጨዋታ በመቻል ሲረታ የጣናው ሞገድም አሸንፏል

እጅግ በከባድ ዝናብ ታጅቦ በተደረገው ጨዋታ መቻል የሊጉን መሪ ሲዳማ ቡናን 3ለ1...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀድያ ሆሳዕና ፣ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ወሳኝ ድል አግኝተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን መርሀግብር ሀዋሳ ከተማ ወደ ሊጉ መሪ የሚጠጋበትን ዕድል...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ፈረሰኞቹ በድል ሲቀጥሉ ንግድ ባንክ እና ድሬዳዋም አሸንፈዋል

ቅዱስ ጊዮርጊስ ተከታታይ ድሉን ወደ ቋቱ ሲከት ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከጨዋታ ብልጫ...

ዋልያዎቹዜናዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን

አንጋፋው አሰልጣኝ በስማቸው የእግር ኳስ ማሰልጠኛ አካዳሚ ሊገነባላቸው ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ አሰልጣኝ ኢንስትራክተር ሰውነት ቢሻውን ለማመስገን እና ዕውቅና ለመስጠት...