መነሻ ገጽ ሀዲያ ሆሳዕና ሀድያ ሆሳዕና ከአሰልጣኙ ጋር ሊለያይ የሚችለው ምን አይነት ነገር ሲከሰት ነው ?
ሀዲያ ሆሳዕናዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ሀድያ ሆሳዕና ከአሰልጣኙ ጋር ሊለያይ የሚችለው ምን አይነት ነገር ሲከሰት ነው ?

አጋራ
አጋራ

ሀድያ ሆሳዕና እያስመዘገበ ካለው ደካማ ውጤት የተነሳ ከዋና አሰልጣኙ ካሊድ መሐመድ ጋር ሊለያይ የሚችልበትን ቅድመ ሁኔታ አውቀናል።

በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ 2008 ላይ የመሳተፍ በለስ ቀንቶት በዛኑ አመት መጨረሻ ላይ በአሰልጣኝ ጥላሁን መንገሻ እየተመራ ከሊጉ መውረድ የቻለ ሲሆን አሰልጣኝ ግርማ ታደሠ በድጋሚ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ሊጉ ከመለሱት በኋላ በፕሪምየር ሊጉ ያለፉትን አመታት እየተሳተፈ ይገኛል። በቀደሙት አመታት ከክፍያ ጋር በተያያዘ ጥያቄ ከሚነሳባቸው እና በድግግሞሽ በሜዳና ከሜዳ ውጪ ባሉ ጉዳዮች ሲታመስ እንመለከተው የነበረው ይህ ክለብ ባለፉት ሁለት የውድድር ዘመናት ግን ከሚነሱበት ጉዳዮች መጠነኛ መሻሻሎችን አሳይቷል። በያዝነው የውድድር ዘመን ባለፈው አመት የአሰልጣኝ ግርማ ታደሠ ረዳት የነበሩትን ካሊድ መሐመድን በመንበሩ በመሾም አመቱን እያሳለፈ የሚገኙት ነብሮቹ በሊጉ ከተደረጉ 30 ጨዋታዎች 35 ነጥብን በመሰብሰብ 15ኛ ደረጃ ላይ በአሁኑ ሰዓት ለመቀመጥ ተገደዋል።

ለውጤት መጥፋቱ እንደ ካርድ እና የተጫዋቾች ጉዳት በምክንያትነት ተደጋግሞ ቢነሳም ክለቡ በተቃራኒው እያስመዘገበው ከሚገኘው ውጤት አንፃር አሰልጣኝ ካሊድ መሐመድ እና ሀድያ ሆሳዕና ሊለያዩ የሚችሉበትን መንገድ አውቀናል። አሰልጣኙ ትላንት ከወላይታ ድቻ ከገጠማቸው ሽንፈት ባሻገር በቀጣይ ከሀዋሳ ከተማ ጋር በ31ኛው ሳምንት የሚኖራቸውን ጨዋታ ማሸነፍ የማይችሉ ከሆነ ብቻ የአሰልጣኙ እና የክለቡ ስንብት የሚረጋገጥ ይሆናል።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...