መነሻ ገጽ ታላቁ ሩጫ ታላቁ ሩጫ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ !
ታላቁ ሩጫዜናዎች

ታላቁ ሩጫ በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ !

አጋራ
አጋራ

 

20ኛው የ 2013 ቶታል ታላቁ ሩጫ በዛሬው ዕለት በደማቅ ሁኔታ ተካሂዶ ሊጠናቀቅ ችሏል ።

በመርሐ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተው ባስጀመሩት መርሀ ግብ የወንዶች እና ሴቶች ውድድር ሲካሄድ በሴቶች ዘርፍ ፅጌ ገብረሰላማ ለተከታታይ አመት ያሸነፈችበትን ውጤት በዛሬው እለት አስመዝግባለች ።

 

አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ 32:32.433 በመግባት ቀዳሚ መሆን ስትችል የንግድ ባንኳ አትሌት መድህን ገ/ስላሴ እና የመከላከያዋ አባይነሽ አየሌ ተከታዩን ደረጃ ይዘው ማጠናቀቅ ችለዋል ።

በወንዶች በተደረገ ውድድር አቤ ጋሻው 28:19.105 በሆነ ደቂቃ በመግባት ውድድሩን በባላይነት ሲያጠናቅቅ ታደሰ ወርቁ እና ምሌሳ መንገሻ በመከታተል በመግባት ውድድራቸው አጠናቀዋል ።

ውድድሩን በአንደኝነት ያጠናቀቁ አትሌቶች ዳጎስ ያለ ሽልማት ሲበረከትላቸው የ አንድ መቶ ሺህ ብር ሽልማት መሸለማቸው ተገልጿል ።

የኮቪድ ጥብቅ ፕሮቶኮልን ተከትሎ የተካሄደው የቶታል የታላቁ ሩጫ እንዳለፈፉት ዓመታት ሁሉ በደማቅ ሁኔታ ሲጠናቀቅ በጎዳና ላይ ሩጫ 12,500 ተሳታፊዎችን በማሳተፍ የዘንድሮውን የውድድር ዓመት በደመቀ መልኩ አካሂዶ አጠናቋል ።

አጋራ

አስተያየት ይስጡ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

ተዛማጅ ጽሑፎች
ኢትዮጵያን በውጪዜናዎች

በካናዳ የኢትዮጵያዊያን የባህል እና ስፖርት ሊግ በይፋ ተመሠረተ

በካናዳ የኢትዮጵያ የባህል እና ስፖርት በሚል ስያሜ ሊግ ተቋቋመ። የኢትዮጵያን ባህል ለአለም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየዲሲፕሊን ውሳኔዎችዲሲፕሊን ውሳኔ

የ32ኛ ሳምንት የዲሲፕሊን ውሳኔዎች

የዲሲፕሊን ውሳኔዎች አህመድ ረሺድ (ድሬደዋ ከተማ) : በኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር 1 እንዲሁም...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሀምራዊ ለባሾቹ እና የጣና ሞገዶቹ ጣፋጭ ሦስት ነጥብን ወደ ቋታቸው ከተዋል

በሊጉ የሳምንቱ የሁለተኛ ቀን ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ባህርዳር ከተማ ወሳኝ...

ዜናዎችየኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግየጨዋታ ዘገባ

ሲዳማ ቡና ሲሸነፍ በተጠባቂው ጨዋታ መቻል በጎል ፌሽታ ነገሌን ረቷል

በሳምንቱ የመጀመሪያ ቀን ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና በሀድያ ሆሳዕና ሽንፈት ሲያስተናግድ...